Thursday, August 30, 2012

ኣረጊት ሰብነትኩም ቐንጥጡ


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

 ናይ’ዚ ትምህርቲ’ዚ መሠረታዊ ዓላማ ክርስቲያን ሰባት ኣብ ሂወቶም መሠረታዊ ለውጢ ንኸምጽኡ ምብርትታዕ እዩ፡፡

  ኣብ ሂወትና ተለዊጦም ክንሪኦም እንደሊ ብዙሓት ነገራት አለዉ፡፡ ዓይነቶም ከዓ ከከም መልክዕና ዝተፈላለዩ እዮም፡፡ ገሌና ደመወዝና ክልወጥ ንደሊ፤ ገሌና ባህርያትና ተመሓይሹ ክንርኢ ንደሊ፤ ገሌና ምስ ካልኦት ሰባት ዘለና ሕርፉፍ ምቅርራብ ተለዊጡ ክንርኢ ንደሊ፤ ገሌና ሓዳርና ስሙር ኮይኑ ክንርኢ ንደሊ፤ ገሌና ሕማቕ እንዳተዛረብና ንሰባት ንቱግ ኢልና እንዳተፃረፍና ተሸጊርና ንኾን፡፡ ኮታስ ብዙሕ ተለዊጦም ክንሪኦም እንደሊ ነገራት ኣለዉ፡፡ እዞም ተለዊጦም ክንሪኦም እንደልዮም ነገራት ተለዊጦም ንምርኣይ ብዙሕ ፃዕሪ ጌርና ንኸውን፡፡ እዚኣቶም ተለዊጦም ንምርኣይ ብዓል ሙያ ኣማኺርና ንኸውን፤ ብዙሓት መጻሕፍቲ ገዚእና ኣንቢብና ንኸውን፤ ብዙሕ ግዜ ንኣምላኽ ለሚንናዮ ንኸውን፡፡ ስለዘይተለወጥና ኸዓ ተስፋ ቖሪፅና ንኸውን፡፡ ለውጢ ምምፃእ ኣብ ህይወትና እቲ ዝኸበደ ነገር ኮይኑ ተሰሚዑና ክኸውን ይኽእል እዩ፡፡

 “ንምንታይ ኣይተለወጥኩን? ንምንታይ ኣምላኽ ፀሎተይ አይሰምዐን?” ኢልና ምሕታት አገዳሲ ጥራሕ ዘይኮነስ ግድን እዩ፡፡ ከምዚ ኢልና እንትንሓትት ፀገምና አበየናይ ቦታ ከምዝነበረ ንምእላሽ መፍትሒኡ እውን ንምንዳይ ኸቢድ ስለዘይኮነ፡፡ እስኪ ንሂወት ያዕቆብ ወዲ ይስሓቕ ብምልዓል እቲ ናሃትና ፀገም ኣበይ ከም ዘሎ ንፈትሾ!

1. ሰብ ሞያ ጥዕና ናይ ሓደ ሰብ ሕማም እንታይ ምኻኑ ምፍላጥ ናይ ሕክምና 50 ምኢታዊ እዩ ይብሉ፡፡ ብመንፅር ክርስትና ከዓ ኣረኣእያ ሰብን ኣረኣእያ እግዚአብሄርን ዝተፈላለየ ስለዝኾነ እግዚኣብሄር በቲ ዝጠቕመና መኣዝን እንትጅምር ንሕና ድማ ኣይኾንን ኢልና በኣንፃሩ ኬድና ክንከውን ንኽእል ኢና፡፡ ንሕና እንሪኦ ደጋዊ መልክዕ እንትኸውን እግዚኣብሄር ግና እቲ ውሽጣዊ ፅባቐ ይርኢ፡፡ እዙይ እውን ካብ ቃል ኣምላኽ ክንርዳእ ንኽእል፡፡ “ኣነ እግዚኣብሄር ከም ኣረኣእያ ሰብ ኣይርእን እየ፡፡ ሰብ ነቲ ኣብ ቅድሚ ዓይኑ ዘሎ እዩ ዝርኢ፤ ኣነ እግዚኣብሄር ግና ልቢ እየ ዝርኢ” ይብል /1ሳሙ.16፡7/፡፡ ስለዚ እቲ ናህና ሕቶ ኣበይ ነበረ? ውሽጥና ንኽልወጥ

Tuesday, August 28, 2012

Kadhannaa Barii (Ganamaa)

Maqaa Abbaa kan Ilmaa kan Afuura Qulqulluu Waaqa Tokko Ameen!

Faarfannaa Daawwit 5
Yaa Waaqayyoo kadhannaa koo dhaggeeffadhu,
Iyya koos hubadhu;
Jecha kadhannaa koos dhaggeeffadhu,
Yaa Mootii koo yaa Waaqa koo,
Maaloo gara keettan kadhannaa koo dhiyeessa hoo.
Bariidhaan sagalee koo dhagayi,
Bariidhaan durakeen dhaabbadha sin eeggadhas.
Ati Waaqa badii hin jaallanne dha hoo;
Warri hamaan si wajjin hin bulani.
Akkasumaan kan boonan ija kee dura hin dhaabbatanu,
Warra hamaa hojjetan mara ni jibbite.
Kan soba dubbatan hunda ni balleessita;
Isa dhiiga dhangalaasuu fi warra gowwomsoota ta’an Waaqayyo ni balaaleeffata.
Ani garuu baay’ina araara keetiin
Gara mana keettan ol-seena;
Siin si sodaachuudhaan gara mana-qulqullummaa
Keettan sagada (ugguma).
Yaa Waaqayyoo sababa diinoota kootiif tolaan na gaggeessi;
Karaa koo dura keetti sirreessi.
Afaan isaanii keessa dhugaan hin jiru,
Onneen isaaniis gatii hin qabu,
Qoonqoon isaanii akka awwaala banamaa dha;
Arraba isaaniitiin ni gowwomsu.
Yaa Waaqayyoo isaanitti murteessi maree isaaniitiinis haa kufani;
Waa’ee baay’ina hammeenya isaaniitiifis isaaniin godaansiisi (hari’i),
Isaanis si gaddisiisaniiru hoo.
Kan sitti amanan martinuu ni gammadu;
Bara baraanis ni gammadu, isaaniinis ni eegda.
Maqaa kee kan jaallatan martinuu siin boonu.
Ati isa qulqulluu ni eebbista hoo;
Yaa Waaqayyoo akka gaachanaa haboodhaan nu marsite.
Galanni Abbaaf Ilmaaf Afuura Qulqulluuf haa ta’u bara baraan Ameen!
Hallee Luyaa galanni Waaqayyoof, Hallee Luyaa yeroo maraa galanni Amaanu’eel Waaqa keenyaaf haa ta’u. Yaa Gooftaa koo Iyyesuus Kiristoos akkan icciitii baruuf kennaa kee naaf laadhu, hammeenya afuuroota hamaa hammeenya isaanii naaf ibsi, gargaarsa Afuura Qulqulluutiin kadhata kootiin yeroon si gaafadhu dura kootii isaan fageessi isaan qaaneessi; kunis araara keetiin naaf haa ta’u, naaf haa raawwatu.
Harmee koo hirkoo koo Giiftii koo dubroo Maariyaam abdiin koo siiyidha kennaa kee isa eebbifamaa amanachuun gara Ilma kee Iyyesuus Kiristoositti akka na haraarsitu sin kadhadha.
Haraarri Waaqummaa Ilma kee akka narraa adda hin baane yeroo mara naaf kadhadhu. Gargaarsi kees akka naa golboobu jaalalli kee akka naaf baay’atu naaf taasisi. Yaa jaallatamtuu gara laafeetti dubroo Maariyaam abdii koo haraarsummaa kee irran taasifadha. Yeroo yerootti eegumsi kee akka narraa adda hin baane ifni kennaa kee naaf haa ifu.
Yaa Waaqayyoo Waaqa moototaa addunyaan osoo hin uumamiin dura kan turte addunyaa dabarsitee bara baraan kan jiraattu Gooftaa uumama maraa aduu guyyaadhaaf ifa; halkan boqonnaa ilma namaatiif kan uumte yaa Waaqayyoo sin galateeffadha; ati halkanicha nagaadhaan dabarsitee gara jalqaba guyyaa kan ta’e ganama kanaan waan na geesseef sin galateeffadha; kadhannaa koo gara si isa Mootii addunyaa tottolchiteettin dhiyeeffadha. Dhugaa isa ta’e beekumsa ifa kee naaf dhiyeessi ibsaa laphee koo naaf ibsi ifni Waaqummaa kee laphee koo keessatti akka naaf ifuuf guyyaan jalqabe kana tolaa fi qulqullummaan akkasumas seera gaariidhaan xumuree gufuu malee jireenya koo akkan dabarsuuf na gargaari. Ati eebbifamaadha hoo kabaja, galata fi sagada Abbaa Ilma Afuura Qulqulluutiif nan dhiyeessa hanga bara baraatti Ameen!
Itti fufa...

Sunday, August 26, 2012

አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ!


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

   ኢትዮጵያዊው ሊቅና ጻድቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ከቅዱስ ያሬድ ቀጥሎ ታላቅ ቦታ የያዘ ኢትዮጵያዊ ሊቅ ነው፡፡  አባ ጊዮርጊስ የተወለደው 1357 . በወሎ ክፍለ ሀገር በቦረና ወረዳ ሰግላ በተሰኘች ቦታ ነው፡፡ ወላጆቹ ልጅ ስለሌላቸው ዘወትር እያዘኑ ወደ እግዚአብሔር ይጸልዩ ነበር፡፡ አባ ጊዮርጊስ የተወለደው በቅዱስ ዑራኤል አብሳሪነት መሆኑን ድርሳነ ዑራኤል ይተርክልናል፡፡ አባቱ ሕዝበ ጽዮን እናቱ አምኃ ጽዮን ይባላሉ፡፡  አባቱ ጠቢብና የመጻሕፍት ዐዋቂ፤ የእግዚአብሔር ወዳጅና በቤተ መንግሥት በነበረችው ድንኳንሥዕል ቤትከሚያገለግሉ ካህናት ወገን ሲሆን የሰግላ ሀገረ ገዥም ነበር፡፡  የአባ ጊዮርጊስን እናት እምነ ጽዮን ከወለቃ /የዛሬው ደቡብ ወሎ፣ ቦረና/  ከሹማምንት ወገን የሆነች ደግ ሰው ነበረች፡፡

 አባ ጊዮርጊስ በመጀመርያ እናቱ ፈሪሐ እግዚአብሔርን እያስተማረች በጥበብና በዕውቀት አሳደገችው፡፡ አባ ጊዮርጊስ የመጀመርያውን የቤተ ክርስቲያን ትምህርት የተማረው ከአባቱ ነበር፡፡ ምክንያቱም አባቱ የመጻሕፍት ሊቅ መሆኑን ስንመለከትና ገድሉም አባ ጊዮርጊስን በተመለከተወሶበ ልሕቀ ሕቀ ወሰዶ ኀበ ጳጳስ ወሴሞ ዲያቆንየሚለውን ስናጤነው አባቱ የመጀመርያውን ደረጃ ትምህርት ካስተማረው በኋላ በ1341 ዓ.ም ወደ ኢትዮጵያ ከመጡትና እስከ ዐፄ ዳዊት ዘመነ መንግሥት ጳጳስ የነበሩት ከአቡነ ሰላማ መተርጕም ዘንድ ወስዶ ዲቁና አሹሞታል ማለት ነው፡፡
                                             
  ዲቁና ከተቀበለ በኋላ ለትምህርት ወደ ሐይቅ እስጢፋኖስ ተላከ፡፡ ወደ ሐይቅ የገባው በዐፄ ዳዊት ዘመነ መንግሥት መሆኑን ገድሉ ይገልጣል፡፡ ሐይቅ እስጢፋኖስ የተለያዩ ሊቃውንት የሚገኙባት፣ በብዙ መጻሕፍት የተሞላችና ዙሪያዋን በሐይቅ በመከበቧ የተማሪን ሳብ ለማሰባሰብ አመቺ የሆነች ቦታ ናት፡፡ አባ ጊዮርጊስ በሐይቅ እስጢፋኖስ ትምህርት አልገባው ብሎ ለሰባት ዓመታት ተቀምጦ ነበር፡፡ አብረውት የሚማሩት ተማሪዎችይህ ትምህርት የማይገባው ስለ ምንድን ነው? በእርሱ ኃጢአት ነው ወይስ በወላጆቹ ?” ይሉት ነበር፡፡ በዚያ ጊዜ የሐይቁ መምህር የነበረው ዐቃቤ ሰዓት ሠረቀ ብርሃን ለአባቱልጅህ ትምህርት አይገባውምና የቤተ መንግሥት ነገር አስተምረውብሎ መለሰው፡፡ አባቱ ሕዝበ ጽዮን ግንአንድ ጊዜ ለእግዚአብሔር ሰጥቼዋለሁ፤ እዚያው ገዳሙን ያገልግልብሎ እንደ ገና ላከው፡፡

 አባ ጊየርጊስ በቀለም ትምህርት እንዲሰንፍ ምክንያት የሆነው ከመማር ይልቅ በሥራ እየደከመ የገዳሙን አባቶች መርዳትና ብሕትውናን ይማርከው ስለ ነበር ነው፡፡ በገዳሙ  እህል በመፍጨት ያገለግል ነበር ፡፡ አባ ጊዮርጊስ እህል ይፈጭበት የነበረውን የድንጋይ ወፍጮ እስከ አሁን በገዳሙ አለ፡፡

  አባ ጊዮርጊስ ዕውቀት ስለ ተሠወረውና ጓደኞቹ በትምህርት ሲቀድሙት ባየ ጊዜ እጅግ አዘነ፡፡ ስለዚህም

Friday, August 24, 2012

ማንም የተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ- የዮሐንስ ወንጌል የ35ኛ ሳምንት ጥናት (ዮሐ.7፡37-ፍጻሜ)!


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

  በ33ኛ ሳምንት ጥናታችን እንደተናገርን አይሁድ የዳስ በዓልን የሚያከብሩት ሰባት ቀን ሙሉ እንደ አንድ ቀን ነው /ዘሌ.23፡34/፡፡ በበዓሉ እኩሌታ ማለትም በአራተኛው ቀንም ጌታ በሕቡዕ ያይደለ በይፋ በስዉር ያይደለ በግልጥ ማስተማሩን መገሰጹን ተመልክተናል፡፡ አሁን ደግሞ በበዓሉ በኋለኛው ቀን፣ የደስታ ቀን ብለው በሚያከብሩበት በመካተቻው፣ በመጨረሻው፣ በመሰባበቻው ቀን እንዲህ ብሎ አሰምቶ ተናገረ፡- ማንም የተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ። በእኔ የሚያምን መጽሐፍ እንዳለ፥ የሕይወት ውኃ ወንዝ ከሆዱ ይፈልቃል” /ቁ.37-38/። እንዲህ ማለቱ ነበር፡- ማንም ጽድቅን የተጠማ ቢኖር፣ ማንም ሕይወትን የናፈቀው ቢኖር፣ ማንም መንግሥተ ሰማያትን መውረስ የሚፈልግ ቢኖር፣ ማንም እኔ የምሰጠውን የጽድቅ ውኃ መጠጣት የሚሻ ቢኖር፣ ማንም እኔ የምሰጠውን ሀብታተ ምሥጢራትን ጸጋውን መቀበል የሚፈልግ ቢኖር… ወደ እኔ ይምጣ፤ በእግረ ሥጋ ሳይሆን በእግረ እምነት ወደ እኔ ይቅረብ፤ በእግረ በቀል ሳይሆን በእግረ ፍቅር ወደ እኔ ይጠጋ፤ ቀርቦም የምሰጠውን ውኃ ይጠጣ፤ መጥቶም ከዙፋኔ የሚወጣውን እንደ ብርሌም ሚያንጸባርቀው የሕይወትም ውኃ ከሚሆን ወንዝ ይጠጣ ይቀበል /Augustine, On the Gospel of St. John, tractate 32:2./፡ ሙሴ ከሰጠው ጊዜአዊ ጥምንም ከሚያረካው ውኃ ተላቆ ይምጣና አማናዊውን የሕይወት ውኃ ምንጭ ዐለት በውስጡ ያኑር፡፡ ይህን እንዴት ማግኘት እችላለሁ ብሎ የሚቸገርም ከቶ አይኑር፡፡ ነቢያት ይወርዳል ይወለዳል ብለው የተናገሩለት፣ ሱባዔ የቆጠሩለት መሲሕ ክርስቶስ እርሱ ነው ብሎ በእኔ ይመንና መጽሐፍ እንደተናገረ የሕይወት ውኃ ወንዝ ከሆዱ ይፈልቃል (በእርሱ ምክንያት ቃሌ ሲነገር ልጅነት ሲሰጥ ብዙዎች ሲያምኑበት ይኖራል)፤ በፈሳሾች አጠገብ እንደሚበቅሉ እንደ አኻያ ዛፎች ይሆናል /ኢሳ.44፡3/፤ ከተድላ ፈሳሽ ይጠጣል /መዝ.36፡8/፤ የሕያዋን ምንጭ የሚሆን መንፈስ ቅዱስ ያድርበታል /ኤር.2፡13/፤ የእግዚአብሔርን ቸርነት ይቀምሳል ያያልም /መዝ.34፡8/፤ በኢዩኤል ነብይ የተነገረው ትንቢት በእርሱ ላይ ይፈጸማል” /ኢዩ.2፡28-32፣ Saint Cyril the Great, Commentary on the Gospel of John, Book 5/፡፡

 ይህም አስቀድመን እንደተናገርን ያመኑበት ሰዎች ሊቀበሉት ስላላቸው ሀብታተ መንፈስ ቅዱስ የተናገረው ነው፡፡ ይህን ያለው ምእመናን በመንፈስ ቅዱስ ስለሚያገኙት ምሥጢር፣ በመንፈስ ቅዱስ ስለሚገኙት ልጅነት ሲገልጽ ነው፡፡ ኢየሱስ ገና ስላልከበረ (ያስተውሉ! ከዚያ በፊት ክብሩ በሰው ዘንድ አልታወቀም አልተገለጠም ነበር ለማለት እንጂ ሎቱ ስብሐትና ክብር አልነበረውም ማለት አይደለም፡፡ በብዙዎች ዘንድ ጌታ መሆኑ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑ የታወቀው ከስቅለቱ በኋላ ከትንሣኤም በኋላ ስለ ሆነ ነው) ስላልተሰቀለ መንፈስ ገና አልወረደም ነበርና /ቁ.39/። ይህ ማለት ግን መንፈስ ቅዱስ ክርስቶስ ከመሰቀሉ በፊት በሰው ልጆች ላይ አልነበረም ማለት አይደለም፡፡ መንፈስ ቅዱስ በነቢያት ነበረ፤ መጽሐፍ እንደተናገረ አስቀድሞ በእመቤታችን ላይ ወርዷል፤ ወንጌል እንደመሰከረ መንፈስ በስምዖን አረጋዊ ላይ ነበረ፤ በነቢይቱ ሀና ላይ ነበረ፡፡ ስለዚህ አሁን እየነገረን ያለው አጠቃላይ በቤተ ክርስቲያን ላይ ከበዓለ ኃምሳ በኋላ ሊሆን ስላለው ሁኔታ ነው /Augustine, tactate 32:7. /፡፡

  ከሕዝቡ አያሌ ሰዎች ይህን ቃል ሲሰሙ፣ “ማንም የተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣ” የሚል የጌታችን የፍቅር ግብዣ ሲያደምጡ በአራት ምድብ ተከፋፈሉ፡፡ በአንደኛው ምድብ የነበሩት ይህ በእውነት ሙሴ እንደ እኔ ያለ ነቢይ ያስነሣልሃል ብሎ የተናገረለት ነቢዩ ነው” አሉ /ዘዳ.15፡18/፤ ሁለተኛው ምድብ የነበሩት፡-ነቢዩ አይደለም ይህ ክርስቶስ ነው” አሉ፤ በሦስተኛው ምድብ የነበሩትና አወቅን ጠነቀቅን ያሉት ደግሞ፡-ክርስቶስ በእውኑ ከገሊላ ይመጣልን? ክርስቶስ ከዳዊት ዘር ዳዊትም ከነበረባት መንደር ከቤተ ልሔም እንዲመጣ መጽሐፍ አላለምን?”  በማለት ጌታ በናዝሬት ገሊላ ማደጉ ናዝሬት ገሊላ የተወለደ ስለመሰላቸው ተደናገሩ /መዝ.132፡11፣ ሚክ.5፡2/። አራተኛው ምድብ ደግሞ ከጸሐፍትና ከፈሪሳውያን ከአለቆቹ ጋር ያበሩና ጌታን ለመግደል የሚያስቡ ሎሌዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ሎሌዎች ክርስቶስን ለመያዝ ወደው ነበር ይዘውም ለአለቆቻቸው አሳልፈው ይሰጡት ዘንድ ሽተው ነበር፡፡ ሆኖም ግን በቃሉ ተማርከው አምነውበታልና አንድም ጊዜው አልደረሰምና ይህን ማድረግ አልተቻላቸውም /ቁ.40-44፣ Saint Cyril the Great, Ibid/፡፡

 አስቀድመን እንደተናገርን የመጨረሻው ቀን ማለት አይሁድ በደስታ የሚያከብሩት ቀን ነው፡፡ ዛሬ ግን ጸሐፍትና ፈሪሳውያን የደስታ ቀን ሊሆንላቸው አልቻለም፡፡ የደስታ ምንጭ የሆነውን ክርስቶስን ሊገድሉበት ፈለጉ እንጂ እርሱን ተቀብለው ደስታቸውን ፍጹም ሊያደርጉት አልቻሉም፡፡ ውስጣቸው በቅንአት ተጠፍሯልና ይህን የክርስቶስ ፍቅር ማየት አልተቻላቸውም፡፡ የደስታ ቀን በሆነው ዕለት መንፈሳዊ ተግባራቸውን ትተው ሊገድሉት የሚፈልጉትን ክርስቶስ ይጠባበቁ ነበር፡፡ ሆኖም ግን እንዳሰቡት አልሆነላቸውም፡፡

  ሎሌዎቻቸው (አራተኛው ምድብ ያልናቸው ናቸው!) ክርስቶስን ሳይዙ በመጡ ጊዜ፣ አስረን እናመጣዋለን ብለው ሄደው አምነው እየተደነቁ በመጡ ጊዜ፡-ለምድነው ያላመጣችሁት?” ብለው ተቈጡዋቸው። ሎሌዎቹ ግን አሳማኝ ምክንያት ነበራቸው፡፡ አለቆቻቸው ባይቀበልዋቸውም እንዲህ ሲሉ ሳይፈሩ አስረድዋቸው፡-አለቆቻችን ሆይ! ይህን ሰው ለምን ይዛችሁት አልመጣችሁም ብላችሁ የምቆጡን አትሁኑ፤ ይህ ሰው እንደተናገረው በዓለም ታይቶም ተሰምቶም ከቶ ከቶ አይታወቅም፡፡ እኛ መጻሕፍትን እናውቃለን ብለን እናስብ ነበር፡፡ ሆኖም ግን ገና አላዋቂዎች መሆናችንን ዛሬ አይተን ተረድተን መጣን፡፡ እርሱ የሚናገረው ነገር ፍጹም መለኰታዊ ቃል ነውና፡፡ ይህ ሰው የሚናገረው ማንም ምድራዊ መምህር ሊያስተምረው ሊናገረው የሚቻለውም አይደለምና፡፡ ስለዚህ ይህን ሰው ፈጽመን ልንገድለው አይገባንም፡፡ በአፉ ተንኰል አላገኘንበትምና እንደ ሕጋችን ንጹሕ ሰው ልንገድል አይገባንም፡፡ እንደውም በሰቂለ ሕሊና ስናስተውለው ስናደምጠው እንደ እግዚአብሔር በኃይልና በሥልጣን ይናገራል እንጂ እንደ ዕሩቅ ብእሲ አይናገርም፡፡ ምክንያቱም ማንም የተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣ ያለ ነቢይ ሰምተንም አይተንም አናውቅምና፡፡ ታላቁ አባታችን ሙሴ እንኳን አንድ ቀንም ቢሆን በእኔ የሚያምን መጽሐፍ እንዳለ፥ የሕይወት ውኃ ወንዝ ከሆዱ ይፈልቃል ሲል አልሰማነውምና፡፡ ይህ ሰው ግን ማንም የተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣ፤ በእኔ የሚያምን መጽሐፍ እንዳለ፥ የሕይወት ውኃ ወንዝ ከሆዱ ይፈልቃል እያለ በሥልጣን ይናገራል፡፡ የሚናገረው ሁሉ ዕሩቅ ብእሲ የሚናገረው አይደለም” ብለው መለሱላቸው /ቁ.45-46፣St. Cyril the Great, Ibid/። ተወዳጆች ሆይ! የክርስቶስን ፍቅር የምታስተውሉ ሁኑ፡፡ ምክንያቱም እነዚህን አለቆች እጅግ ከማፍቀሩ የተነሣ እንዲጠፉበትም ካለመፈለጉ የተነሣ ይመለሱለት ዘንድ ልባቸው ደንዳና ሆነ እንጂ ሊያደምጥዋቸው በሚችሉ ሰዎች ሲያስረዳቸው ነበርና፡፡

  ስለዚህ አለቆቹ ጭራሽ እንዲገባቸው አልፈቀዱምና ባሰባቸው፡፡ ሎሌዎቻቸውንም፡-እናንተ ደግሞ እንደነዚያ ሐዋርያት ሳታችሁን?” አልዋቸው /ቁ.47/፡፡ በክርስቶስ ማመን መሳት ነው አሉዋቸው! የሕይወትን ውኃ ማግኘት መታለል ነው አሉዋቸው፡፡ ከሞት ወደ ሕይወት መሻገር ሞት ነው አልዋቸው፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን ሕዝቡን እንዲህ አሳምኖ እንዳይወስድባቸው በመጨነቅ ለመሆኑ ከተሳሳቱት ሕዝብ በቀር ከአለቆች ወይስ ከፈሪሳውያን በእርሱ ያመነ አለን?” ብለው ጠየቁዋቸው /ቁ.48/፡፡ አሁንም ብስጭታቸውን ቀጠሉና አስተምረውት የማያውቁትን ሕዝብ ሕግን ኦሪትን የማያውቀው ይህ ሕዝብ ርጉም ነው” ብለው ሕዝቡን መሳደብ ጀመሩ፤ ሎቱ ስብሐትና ክርስቶስን “ዕሩቅ ብእሲ” አድርገውት ፍጡርን የሚያመልኩ እነዚህ የተረገሙ ናቸው አሉ /ቁ.49/። የአምላካቸውን ድንቅ ሥራ አይተው ያመኑትን ሕዝብ ሕግን የማያውቁ እያሉ ወቀስዋቸው፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ ሕዝቡ አምላኩን አውቆ ስላመነበት ሊበሳጩ አይገባም ነበር፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ ሕግን የማያውቁና የተረገሙ ክርስቶስንም ከማመን የዘገዩ እነርሱ ራሳቸው ነበሩ /St. John Chrysostom, Homily 52/፡፡

 የሚደንቀው ግን ይህን አላዋቂነታቸው ይነግራቸው ዘንድ እግዚአብሔር በመካከላቸው ምስክር ማስቀመጡ ነው፡፡ እርሱም በሌሊት ቀድሞ ወደ ጌታ መጥቶ የነበረው የማታው ተማሪ ኒቆዲሞስ ነው /ዮሐ.3፡2/፡፡ ብስጭታቸውን በሰማ ጊዜ፣ ሕዝቡን አላዋቂ ሲሉት ባደመጠ ጊዜ፡-ኦሪታችን ሥራውን አስቀድሞ ከእርሱ ሳይሰማ ምንስ እንዳደረገ ሳያውቅ ሳይመረምር በሰው ላይ ይሙት በቃ ይፈርዳልን?” አላቸው /ቁ.50-51/ እውነት ነው! ኦሪት “ንጹሑን ሰው አትግደል” ትላለች /ዘዳ.19፡16-21/፡፡ ተራውን ሕዝብ በሕግ አፍራሽነትና በአላዋቂነት እየፈረጁና እየረገሙ እንጠብቀዋለን የሚሉትን ሕግ የሚያፈርሱት እነርሱ ራሳቸው ነበሩ፡፡ ስለዚህ አላዋቂዎች እነርሱ መሆናቸውን ኒቆዲሞስ ይነግራቸው ነበር፡፡ እነርሱ ግን አሁንም በኒቆዲሞስ ንግግር ተበሳጩ፡፡ “ለምን ታድያ ከገሊላ መጣ?” ብለው ከመጠየቅ ይልቅ ኒቆዲሞስን መስደብ ጀመሩ፡፡አንተም ደግሞ ከገሊላ ነህን? ነቢይ ከገሊላ እንዳይነሣ መርምር አንብብና እይ” ማለትን አስቀደሙ /ቁ.52/። ለምን ከገሊላ መጣ ብለው ቢጠይቁ ግን ክርስቶስ እርሱ ኢየሱስ ናዝራዊ ይባል ዘንድ በናዝሬት ገሊላ ያደገ ነገር ግን በቤተልሔም የተወለደ መሆኑን ባወቁ በተረዱ ነበር /ማቴ.2፡1 እና 23/፡፡ እነርሱ ግን ለስድብ ተቻኮሉ፡፡ በዚህ ንግግራቸው ኒቆዲሞስን እንደ አላዋቂ አድርገው በማየት መናቃቸው ነበር /St. John Chrysostom, Ibid/፡፡

 በመጨረሻም ምንም ሳይስማሙ  ተለያይተው እያንዳንዳቸው ወደየቤታቸው ሄዱ /ቁ.53/።

  ተወዳጆች ሆይ! ቅናት ክፉ ነው፡፡ ቅናት ዓይነ ልቡናን ያሳውራል፡፡ ቅናት ክርስቶስን ከማየት ይከለክላል፡፡ ቅናት ከዐለቱ (ከክርስቶስ) የሕይወት ውኃ እንዳንጠጣ ያደርጋል፡፡ ሀብታተ መንፈስ ቅዱስን እንዳንቀበል ያደርጋል፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞን “ጕድጓድን የሚምስ ይወድቅበታል፤ ድንጋይንም የሚያንከባልል ይገለበጥበታል” እንዳለ ቅናት የሚጐዳው ቅናተኛውን ነው /ምሳ.26፡27/፡፡ ቅናት ስለ እኛ የተቸነከረው በደምም የጨቀየውን ያ የፍቅር እጅ እንዳንመለከት ያደርጋል፡፡ ቅናት ተድላ መንግሥተ ሰማያትን እንድናጣ ያደርጋል፡፡ ወዮ አባት ሆይ! ራሳችንን እንዳንጐዳ በቅዱስ መንፈስህ ምራን! ከቅናት ከበቀል ጠብቀን! ፈሪሳዊ ቁጣና ብስጭት ከእኛ የራቀ ይሁን! አሜን! 

FeedBurner FeedCount