Tuesday, October 30, 2012

ጌታ ሆይ አምናለሁ -የዮሐንስ ወንጌል የ40ኛ ሳምንት ጥናት (ዮሐ.9)


       በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
  በምዕራፍ 8 እንደተመለከትን ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሚነግራቸውን ነገር ከማመን ይልቅ አይሁድ “ጋኔን አለብህ” /8፡48/ ብለው በድንጋይ ሊወግሩት ሽተው ነበርና አንድም “አብርሃም ሳይወለድ እኔ አለሁ” /8፡58/ ብሏቸው ነበርና ቁጣቸውን አብርዶ ቀዳማዊነቱን በገቢር (በሥራ) ያስረዳቸው ዘንድ ወደደ /መዝ.51፡4/፡፡ ስለዚህም ሲያልፍ ከመወለዱ ጀምሮ ዕውር የሆነውን ሰው (ሲለምን) አየ /ቁ.1/። ይህ ዐይነ ሰውር ሰው የዓይን ምልክት እንኳን አልነበረውም፡፡ እንዲሁ ልሙጥ ግንባር ነበረው እንጂ፡፡ ስለዚህ ሰውዬው ሳይሆን ክርስቶስ አየው፡፡ ደቀ መዛሙርቱም ክርስቶስ ዕዉሩን በልዩ እይታ (በፍቅርና በሐዘኔታ) እንዳየው አስተዋሉ፤ ደነቃቸውም፡፡ አስቀድሞ መጻጉዑን ሲፈውሰው፡- “ዳግመኛ እንዳትበድል” ብሎት ስለነበረ /5፡14/ “ይህ ዕዉር ሆኖ የተወለደውም ዕዉርነቱ ከበደል የተነሣ ነው ማለት ነው” ብለው አሰቡ፡፡ አሳባቸው ግን ግራ አጋባቸው፡፡ ስለዚህም፡-  መምህር ሆይ፥ ይህ ሰው ዕውር ሆኖ እንዲወለድ ኃጢአት የሠራ ማን ነው? እርሱ ነው ወይስ ወላጆቹ?” ብለው ጌታን ጠየቁት /ቁ.2/። ጌታችንም፡-እርሱ ወይም ወላጆቹ ኃጢአት አልሠሩም፡፡ ምክንያቱም እያንዳንዱ ሰው በራሱ ኃጢአት ይቀጣል እንጂ አባት ስለ ልጅ ልጅም ስለ አባት አይቀጣምና /ዘዳ.24፡16/፡፡ ታድያ እርሱ ነውን? ብትሉም አይደለም እላችኋለሁ፡፡ እንግዲያ ስለምን ዓይነ ስውር ሆነ? ብትሉም የእግዚአብሔር ሥራ (አስቀድሞ አዳምን ከምድር አፈር የፈጠርኩት ቀዳማዊ የምሆን እኔ መሆኔን) በእርሱ እንዲገለጥ ነው እላችኋለሁ /St. Ephrem the Syrian, Commentary on Tatation’s Diatessaron, 28 /፡፡

Sunday, October 28, 2012

ምክረ አበው ቁጥር አራት


ልጆቼ! ሓኪሞች ብትሆኑ፣ መሀንዲሶች ብትሆኑ፣ የሽመና ሠራተኞች ብትሆኑ፣ መርከበኞችም ብትሆኑ መልካም ነው፡፡ ይህን ጥበብ መማራችሁም ጥሩ ነው፡፡ እኔ ግን ከዚህ የበለጠ ጥበብ አሳያችኋለሁ፡፡ በዚህ (በተማራችሁት ምድራዊ) ጥበባችሁም ሌላ ጥበብ ትማሩበት ዘንድ እማልዳችኋለሁ፡፡ ሰማያዊን ጥበብ! ከላይ በገልጽኩላችሁና እናንተ በተማራችሁት ጥበብ ተጠቅማችሁ ገንዘብ ማግኘታችሁ አይቀርም፡፡ በዚህ ገንዘባችሁ ግን ድሆችን መርዳት ልመዱበት፡፡ ይህ የምነግራችሁን ጥበብ እንደ ቀላል የምታዩት አትሁኑ፡፡ መሀንዲሶች ብትሆኑ በምህንድስና ጥበባችሁና እውቀታችሁ በዚህ ምድር የሚያማምሩ ቪላ ቤቶችን ልትሠሩ ትችላላችሁ፡፡ በምነግራችሁ ጥበብ ግን
በመንግሥተ ሰማያት ውስጥ የዘላለም ቤታችሁን ትሠራላችሁ፡፡ በዚህ ምድር ለምትሠሩት ቤታችሁ በጣም ብዙ ወጪ ብዙም ድካም ይጠይቃችኋል፡፡ በምነግራችሁ ጥበብ ግን ብዙ ልፋት የለውም፡፡ ወጪአችሁ መልካምና ፈቃደኛ መሆን ብቻ ነው፡፡ በዚህ ምድር ለምትሠሩት ቤት የተለያዩ ዓይነት ብረቶችና ማቅለጫዎች እንዲሁም የከበሩ ድንጋዮችን ትጠቀማላችሁ፡፡ በምነግራችሁ ጥበብ ግን ይህ ሁሉ አያስፈልጋችሁም፡፡ የሚያስፈልጋችሁ ብሎን ወይንም ብረት ወይንም የከበረ ድንጋይ ሳይሆን መልካም ምግባራችሁና በጎ ፈቃዳችሁ ብቻ ነው፡፡

Friday, October 26, 2012

ቅዱስ እሰጢፋኖስ

               በዲ/ ሽመል መርጊያ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
  
 በሐዋርያት ስብከት ቤተ ክርስቲያን ስትስፋፋ በትምህርታቸውና በተአምራታቸው ተስበው ወደ ክርስትና እምነት የተመለሱ ከአይሁድና ከአሕዛብ ወገን የሆኑ ክርስቲያኖች መሬታቸውንና ጥሪታቸውን በመሸጥ  ያላቸውን ሀብት አንድነት በማድረግ በኢየሩሳሌም የአንድነት ኑሮን ይኖሩ ነበር፡፡ በኅብረትም የሐዋርያት ትምህርትን በመስማትና  በጸሎት ይተጉ እንዲሁም ማዕድን በመባረክ በጋራ ይመገቡ ነበር፡፡ መጽሐፍ ቅዱስምአንድ ልብና አንዲት ነፍስ አላቸው በማለት (የሐዋ.432) ስለአንድነታቸው ፍጹምነት ይነግረናል፡፡

Tuesday, October 23, 2012

ሞትን መፍራት ማቆም የሚቻለው እንዴት ነው?



በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
 
ጥያቄ፡- እሞታለሁ ብዬ ሳስብ በጣም እጨነቃለሁ፡፡ እናቴ እንደነገረችኝ ከሆነ ሞትን መፍራት የጀመርኩት ገና ከልጅነቴ ጀምሬ ነው፡፡ አሥራ ሁለተኛ ክፍል ሳለሁ በጣም ከምቀርባቸው ጓደኞቼ መካከል ከአንዱ ጋር ተጣላሁና ሳልታረቀው በሳምንቱ ሞተ፡፡ በጊዜው በጣም ጸጸተኝ፡፡ ሞትን ባሰብኩ ቁጥር የሚታየኝ ያ ሳልታረቀው የሞተው ልጅ ነው፡፡ የመፍራቴ መጠንም በእድገቴ ልክ እየጨመረ ነው፡፡ ሌሊት ላይ ባንኜ “አሁን ብሞትስ?” ብዬ እጨነቃለሁ፡፡ ንስሐ ብገባም ፍርሐቱ ሊለቀኝ አልቻለም፡፡ “ሰው ሞተ” ሲባልም በጣም እደነግጣለሁ፡፡ የምደነግጠውና የምፈራው ግን ሰውዬው ስለሞተ ሳይሆን “እኔም እኮ እሞታለሁ” ብዬ ነው፡፡ እባካችሁ በጣም ጨንቆኛልና ሞትን መፍራት ማቆም የሚቻለው እንዴት ነው?
                             እኅታችሁ ኤልሣቤጥ ነኝ ከአ.አ. 

ምላሽ፡-ውድ ጠያቂያችን! የእግዚአብሔር ፍጹም ሰላምታ ባለሽበት ይድረስሽ፡፡ ለጠየቅሽን ጥያቄ የቻልነውን ያህል ለመርዳት መጻሕፍተ ሊቃውንትን አገላብጠን ያገኘነውን መልስ እነሆ ብለናል፡፡ እንደ ጠቋሚ ይረዳሻል ብለንም እናምናለን፡፡ ከቻልሽ አስቀድመሽ በጸሎት ጀምሪና በተመስጦ ሆነሽ አንቢው፡፡ መልካም ንባብ!

ከማኻ ዝበለ መሓሪ መን እዩ?


በስመ ኣብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኣሓዱ ኣምላክ ኣሜን!

ናይዛ ትምህርቲ እዚኣ ቐንዲ ዕላማ ኩላትና ምሕረት ምግባር ንኽንለማመድ ምትብባዕ እዩ፡፡
ነዚኣ ቃል እዚኣ ዝተዛረባ ማኅሌታይ ኣቦና ቅዱስ ያሬድ እዩ፡፡ ቅዱስ ያሬድ ምሕረት እግዚኣብሄር ኣብ ብሉይ ኪዳን ብዕምቆት እንዳስተንተነ የመስግን፤ ይዝምር ከኣ፡፡ ኣስፍሕ ኣቢሉ ክገልፆ እንተሎ “ቃል ኪዳንካ ምስ ኖህ ዘፅናዕካ፣ ንእስራኤላውያን ካብ ሰማይ ማና ኣውሪድካ ዝመገብካ፣ ንምድሪ ጽጌሬዳ ዕንበባን ፍርያትን ሂብካ ፍጥረት ኩሉ እትምግብ፣ ንሰማይን ምድርን ዝፈጠርካ፣ ኩሉ ፍጥረት ብተስፋ ንኣኻ ዝጽበ ከማኻ ዝበለ መሓሪ መን እዩ?” ይብል፡፡ ዋላ ሓደ!

ምሕረት ማለት ቅፅዓት ንዝግብኦ ገበነኛ ርህራሄ ምግባር እዩ /መዝ.51፡1፣7-8/፡፡ ፍቱዋት! ከም ኣበሳና እንተንፍደ ከምቲ ቅፅዓት ዝግበኣና ከኣ እንተንኽፈል ነይርና ኣብ ሓንቲት ሰዓት ጥራይ ክንደይ ጊዜ ምሞትና? እስቲ ካብ ዝወግሕ ጀሚሩ ክሳብ እዛ ሕጂ ዘለናያ ደቒቓ ጥራሕ ክንደይ ግዘ አበስና? እሞ ኣምላኽናኸ ክንደይ ግዘ ሓለፈና? ልቢ ኣምላኽ ዳዊት ነዚ እንዳስተንተነ እንትዝምር ከምዚ ይብል፡- “እግዚኣብሄር ርህሩህን መሓርን እዩ፤ ንኹራ ደንጓዪ፤ ብምሕረት ድማ ምሉእ እዩ፡፡ መግናሕቱ ንግዚኡ እዩ፤ ንዘልኣለም ከኣ ኣይቕየምን እዩ፡፡ ከም መጠን ሓጢኣትና ኣይቀፅዓናን እዩ፤ ከም መጠን አበሳና ድማ ኣይፈድየናን እዩ፡፡ ሰማይ ካብ ምድሪ ልዕል ከም ዝብል ከምኡ ምሕረቱ ኣብ ልዕሊ እቶም ዝፈርሕዎ ዓብዪ እዩ፡፡ ምብራቕ ካብ ምዕራብ ከም ዝርሕቕ ከምኡ ኣበሳና ኻባና ኣርሐቐ” /መዝ.103፡8-12/፡፡ 

እግዚኣብሄር ወልድ ኣብ ደንበ ማል ዝተወልደ፣ ገና ብዕሸሉ እንተሎ ኣብ ሕቑፊ ኣዲኡ ዝተሰደደ፣ በኳሩ እኳ መሕደሪ ጕድጓድ እንዳሃለወን ንሱ ግና ርእሱ ዘፅግዓላ እንተይሃለዎ ከርተት ዝበለ፣ ኣብ መስቀል ዕርቃኑ ወፂኡ ስሌና ዝሓመመን ዝተሳቐየን፣ ብመወዳእትኡ ከኣ ብኣሰቃቒ ሞት ዝሞተ ንዓለም ብምልኡ ምሕረት ክገብረሉ ስለ ዝፈተወ እዩ /ኤፌ.2፡4-5፣ 1ጴጥ.1፡3፣ ሮሜ.5፡6-10/፡፡ ናይ ኣምላኽ ምሕረቱ ካብ ሕሊና ሓሳብ ኩሉ ዝበዝሕ እዩ /ዘኅ.14፡18/፤ ክሳብ ሰማያት ዝበፅሕ ሰፊሕ እዩ

Thursday, October 18, 2012

ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ


  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

 ባለፈው ዝግጅታችን ስለቅዱሳን ሐዋርያት አጠቃላይ መግቢያ አቅርበን በቀጣይነት ደግሞ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የእያንዳንዱን ሐዋርያ የተጋድሎ ሕይወት በዝርዝር እንደምናቀርብ ቃል ገብተን ነበር (የባለፈውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ በመሆኑም ለዛሬ የሐዋርያት አለቃ የሆነውን የሐዋርያው የቅዱስ ጴጥሮስን ሕይወትና ተጋድሎ እነሆ ብለናል መልካም ንባብ።

FeedBurner FeedCount