Wednesday, April 30, 2014

መንፈሳዊ ሕይወት ከትንሣኤ እስከ ጰራቅሊጦስ - ክፍል ፪



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ ፳፪ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
 ውድ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች! በክፍል ፩ ትምህርታችን ከትንሣኤ እስከ ጰራቅሊጦስ ባለው እሑድ ለምን ሱባኤ እንደማይገባ፣ ሰይጣን ይኽን ዓላማ እንዴት እንድንስተው እንዳደረገን፣ በመጨረሻም ይኽን የዲያብሎስን ደባ እንደምን ከንቱ ማድረግ ይቻለናል የሚል ጥያቄ አንሥተን ነበር ያቆምነው፡፡ እስኪ ካቆምንበት እንቀጥልና ለዚኽ ይረዳን ዘንድ አንድ ኃይለ ቃልን መነሻ በማድረግ ለመማማር እንሞክር፡፡ እግዚአብሔር ዓይነ ልቡናችንን ያብራልን፡፡ አሜን!!!

Monday, April 28, 2014

መንፈሳዊ ሕይወት ከትንሣኤ እስከ ጰራቅሊጦስ - ክፍል ፩

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ ፲፱ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
  የዚኽ ትምህርት መሠረታዊ ዓላማ ክርስቲያኖች ከትንሣኤ እስከ ጰራቅሊጦስ ባለው ወራት ውስጥ መንፈሳዊ ሕይወታቸው እንዳይቀዘቅዝ ማበረታታት ነው፡፡
  በቤተ ክርስቲያናችን ሥርዓት መሠረት ከትንሣኤ እስከ ጰራቅሊጦስ እሑድ ባለው ወራት ረቡዕንና ዓርብን ጨምሮ አይጦምም፤ አይሰገድምም፡፡ ይኽም ሠለስቱ ምዕት በ፫፻፳፭ ዓ.ም. በጉባኤ ኒቅያ ሲሰበሰቡ በኻያኛው ቀኖኗቸው የወሰኑት ቀኖና ነው /ሃይ.አበ.፳፡፳፮፣ The Oxford Dictionary of the Christian Church, pp 1250, 1738/፡፡ ይኽን ቀኖና ሲወስኑም ያለ ምክንያት አይደለም፤ ይኽ ወራት ከትንሣኤ ዘጉባኤ በኋላ ያለውን ሕይወታችን የሚያሳይ ስለኾነ ነው እንጂ፡፡ ከትንሣኤ ዘጉባኤ በኋላ ፈቃደ ሥጋን ለፈቃደ ነፍስ ለማስገዛት ተብሎ የሚደረግ ጦምም ኾነ ስግደት የለም፡፡ ሥጋ ሙሉ በሙሉ በዲያብሎስ ከመፈተን፣ ከእግዚአብሔር ውጪ የኾነ ሌላ ሐሳብን ከማሰብ ነጻ የሚወጣበት ወራት ነው፡፡ በዚያ ሰዓት ፈቃደ ሥጋ ከፈቃደ ነፍስ ጋር የተስማማ ነው፡፡ ሥጋ ሙሉ ለሙሉ ከድካሙ ነጻ ስለሚኾን እግዚአብሔርን ለማመስገን ትጉኅ ነው፡፡ እንደ አኹኑ እንቅልፍ እንቅልፍ አይለውም፤ ዘወትር የቅዱሳን መላእክትን ምግብ ለመብላት ማለትም ለማመስገን የተዘጋጀ ነው እንጂ፡፡

Friday, April 18, 2014

በዓለ ትንሣኤ

በገብረ እግዚአብሔር
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ ፲፩ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
የዚኽ ትምህርት መሠረታዊ ዓላማ ክርስቲያኖች ክርስቶስን መስለው እንዲነሡ ማበረታታት ነው፡፡
 በክርስትና ታሪክ፥ የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል ትልቁና ጥንታዊው ነው፡፡ በዓሉ በዓቢይ ጾም፣ በሰሙነ ሕማማት፣ በአክፍሎት እንዲኹም ከትንሣኤ እስከ ጰራቅሊጦስ ባለ የደስታና የሐሴት ወራት እንዲታጀብ መደረጉም ይኽን ታላቅነቱንና ጥንታዊነቱን የሚያስገነዝብ ነው፡፡ ምዕራባውያን ከትንሣኤ ይልቅ የልደትን በዓል በደመቀ አኳኋን ሲያከብሩ የምሥራቅ አብያተ ክርስቲያናት ግን ትንሣኤን ርእሰ በዓላት አድርገው ያከብሩታል፡፡

Wednesday, April 16, 2014

"ዘበተከ እምኔነ ኩሎ ማእሰረ ኃጣውዒነ በህማማቲከ ማኅየዊት ወመድኃኒት"


በክፍለ ሥላሴ
 (መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ 8 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን


የኃይሉ ጥበብና ችሎታው ከፍጡራን ኅሊና በላይ የሆነ የቅዱሳን አምላክ ፈጣሪያችን ሰውን በፈቀደለት መንገድ እንዲመራና መንግስቱን እንዲወርስ የቅዱሳን እጆቹ የግብር ውጤት አድርጎ አበጀው:: ግና ህግን አፍርሶ በፈጣሪው ተከሶ እግዚአብሔር = አባቱን : ልጅነት= ሀብቱን : ገነት= ርስቱን..... ያጣው የሰው ልጅ መርገምን ወርሶ ቁርበት ለብሶ ወደ ምድር ተሰደደ:: በዚህ በሥጋ ከተፈረደበት የመቃብር ግዞቱ ላይ በሲኦል የነፍስ ርደት ስላገኘው የሞት ሞትን ሞተ እንላለን:: ቅዱስ ዳዊትም "ሰው ግን ክቡር ሆኖ ሳለ አያውቅም እንደሚጠፉ እንስሶች መሰለ።" (መዝ.48:12) ያለው የቀድሞ ክብሩን ከኋላ ግብሩ ጋር እያጻጸረ ሲያመለክተን ነው:: ይህንን የነቢዩን ቃል አብራርቶ የሚያስረዳ መልዕእክት በቅዳሴ አትናቴዎስ ላይ እናገኛለን እንዲህ ይላል ሊቁ "ሰብሰ እንዘ ንጉሥ ውእቱ ኢያእመረ" ዳዊት ክቡር ያለው የክብሩ መገለጫ ንግሥናው ነው ግን ያንን ያላወቀው የሰው ልጅ ምን እንዳገኘው ተመልከቱ "አህሰረ ርእሶ በፈቃዱ ወኮነ ገብረ ወመለክዎ እለ ኢኮኑ አጋእዝተ" አዎ ራሱን በፈቃዱ አሰረ ባርያ ሆነ መግዛት መፍጠርና ማስተዳደር ለባህሪያቸው የማይስማማቸውን የሚያመልክ ሆነ:: ከዚህ ጊዜ አንስቶ ለአምስት ሺህ ከአምስት መቶ ዓመታት የቀድሞ ጠላት ዲያቢሎስ ሰውን አስሮ "በግብርናት" የሚገዛው ሆነ::

Saturday, April 12, 2014

ሰሙነ ሕማማት



በሙሐዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረት
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ 5 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 በጥንታውያን አብያተ ክርስቲያናት እጅግ ከሚወደዱ እና ከሚናፈቁ ወቅቶች አንዱ ሰሙነ ሕማማት ነው፡፡ በዕለተ ሆሳዕና ጀምሮ በዕለተ ትንሣኤ የሚጠናቀቀው እጅግ ላቅ ያለ መንፈሳዊ ሕይወት የሚታይበት ጊዜ ነው፡፡ በላቲን Hebdomas Sancta or Hebdomas Maior በግሪክ ደግሞ γία κα Μεγάλη βδομάς, Hagia kai Megale Hebdomas  ታላቁ ሳምንት ተብሎ ይጠራል፡፡ በኛ ደግሞ ሰሙነ ሕማማት፡፡

Tuesday, April 8, 2014

ሆሳዕና ዘሰንበተ ክርስቲያን



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ 4 ቀን 2006 ዓ.ም)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 በዋዜማው ማለትም ቅዳሜ ማታ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ለማኅሌት ደውል ከተደወለ በኋላ ይገባሉ:: ከቅዱስ ያሬድ መጽሐፍትና ከሌሎችም በመላእክት ዜማ ዕለቱን የሚያነሳ ቀለም (ትምህርት) እያነሱ ያድራሉ:: ከዚህ በኋላ ጠዋት ለቅዳሴ ሰዓቱ ሲደርስ ሊቃውንቱተበሀሉ ሕዝብ በበይናቲሆሙ እንዘ ይብሉ ዓይ ውእቱ ዝንቱ ንጉሠ ስብሐት እስመ ውእቱ እግዚአ ለሰንበት ቦአ ሃገረ ኢየሩሳሌም በፍስሐ ወበሰላም- ሕዝቡም እርስ በእርሳቸው ተባባሉ እንዲህ እያሉ ይህ የምሥጋና ንጉሥ ማነው? እርሱ የሰንበት ጌታ ነውና፤ በደስታና በሰላም ወደ ኢየሩሳሌም ሃገር ገባ::” የሚለውን የዕለቱን የጾመ ድጓ ክፍል ይቃኛሉ::

ኒቆዲሞስ ዘቀዳሚት ሰንበት (ሆሳዕና)



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ 3 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 በአብና በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም፣ አንድ የናዝራውያን አምላክ፣ የማይለወጥ የሃይማኖት ምሰሶ፣ የማይፍገመገም የመርከባችን አለቃ፣ የማይጨልም የፋናችን ብርሃን፣ ከዘመናት በፊት በሕልውና አንድ የሆነ፣ በስምና በሥልጣን የሠለጠነ፣ የመለኮቱ አንድነት የማይለወጥ፣ የመንግሥቱ ስፋት የማይወሰን፣ የብልጥግናው ክብደት የማይለካ እርሱ በሰላም ይጠብቀን::

ኒቆዲሞስ ዘዓርብ (ሆሳዕና)



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ 2 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 በአንድነት በሚመሰገን፣ በአንድነትም በሚለመን፣ በአንድነት በሚሰበክ፣ አንደበት ሁሉ የሚገዛለት፣ ጉልበትም ሁሉ የሚሰግድለት፣ ምሥጉን አምላክ በሆነ በእግዚአብሔር ስም፣ በመጽሐፍ ራስ ሁሉ ላይ በጥበብ ቁጥር በእርሱ ስምና በመስቀሉ ምልክት በማማተብ ሰላምታ ይድረሳችሁ:: (መጽሐፈ ምሥጢር)

ኒቆዲሞስ ዘሐሙስ (ሆሳዕና)



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ 1 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 ዙፋኑን በሚንቦገቦግ የእሳት ሰረገላ ላይ ያደረገ፣ በእሳት መጋረጃዎች የሚሰወር፣ በምሥጋናም መብረቅ የሚጋረድ፣ በኪሩቤል የሚመሰገን፣ በሱራፌልም የሚወደስ እስራኤል ያመሰገኑት አንድ አምላክ በሥልጣንና በቻይነት የሰለጠነ በሆነ በእግዚአብሔር ስም ሰላም ይሁንላችሁ:: (መጽሐፈ ምሥጢር)

FeedBurner FeedCount