Saturday, November 15, 2014

አብሬሽ ልመለስ



በዲ/ን ዶ/ር ቴዎድሮስ በለጠ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ቅዳሜ ኅዳር 6 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

ከክብር ማረፊያው ከገሊላው ቤትሽ
ሰማሁ መፍለስሽን ወደ ግብጽ ወደ ኩሽ
ፀሐይ ሲያከትራት ያቺን የበረሃ ዖፍ
ጼዋዌን ስትናፍቅ ላንዲት ቅጽበት ሳታርፍ
ሰማሁኝ ስደቷን መጠጊያ ሳታገኝ በልቤ ላይ ስታልፍ

Wednesday, November 12, 2014

ወደ እግዚአብሔር ለመድረስ (ደረጃ አንድ)

በዲ/ ሳምሶን ወርቁ

  (መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐሙስ ኅዳር ቀን፣ ፳፻፯ ..)- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
 
ለዓለም ጀርባችንን እንስጥ

 እግዚአብሔር ለሰው እውቀትና ነጻ ፈቃድ ሰጥቶ አክብሮ ፈጠረው፡፡ አንዳንዶች ነጻ ፈቃዳቸውን ተጠቅመው እውነተኛ የእግዚአብሔር ወዳጅ ሆኑ፤ አንዳንዶች በስንፍናቸው ነጻ ፈቃዳቸውን ተጠቅመው ልግመኛ ክፉ አገልጋይ ሆኑ፡፡
ቅዱስ ዮሐንስእኔ ከየትኛው ነው የምመደበው? ከእውነተኞቹ አገልጋዮች ወይስ ከሀሰተኞቹ?” ብለን ራሳችንን እንጠይቅ ይለናል፡፡ የተጠመቀ ሁሉ የእግዚአብሔር መንግሥት ወራሽ አይደለም፣በጠባቡ ደጅ የሚገባ ሁሉ በጽናት ላይጓዝ ይችላል (ማቴ 713)፡፡ መጠመቃችን በራሱ ብቻውን ወደ መንግሥተ ሰማያት ለመግባታችን ዋስትና አይደለም፡፡ ጥምቀት (ከኃጢያትና በኃጢአት ከመጣብን ፍዳ መዳን) ወደ ድኅነት የመግቢያ በር እንጂ ብቻውን የድኅነት መደምደሚያ አይደለም፡፡ መንፈሳዊ ሕይወትን መጀመራችን በራሱ ፍጻሜአችንን መልካም ያደርጋል ለማለት አያስችለንም፡፡  ይህ ማለት ያመነ ሊክድ ያወቀ ሊጠራጠር እና በጎ አገልጋይ ወደ ክፉ ባሪያነት ሊለወጥ የሚችልበት እድል ዘወትር አለ፡፡ አንዳንዶች በመጠመቃቸው ብቻ እንደሚድኑ የሚያስቡ አሉ፡፡ ነገር ግን ጥምቀት ብቻውን ከእግዚአብሔር የተገባልንን ቃልኪዳን አያስጠብቅልንም፡፡ ስለዚህ የመንፈሳዊ ሕይወታችንን ትክክለኛ አቅጣጫ ልንመለከት ልንመረምር ይገባል፡፡ማንም ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማይ አይገባም የአባቴን ፈቃድ የሚፈጽም እንጂእንዲል (ማቴ 721)፡፡

Monday, November 10, 2014

ለይሖዋ ምስክሮች ኑፋቄ የተሰጠ ምላሽ (ክፍል ሦስት)

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ማግሰኞ ኅዳር 2 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
የሥላሴ ትምህርት በቅድመ ኒቅያ አበው
ውድ የመቅረዝ ተከታታዮች እንደምን ሰነበታችኁ? በጥያቄና መልስ ዓምዳችን ለይሖዋ ምስክሮች የስሕተት ትምህርት ኦርቶዶክሳዊ ምላሽ መስጠት ከዠመርን የዛሬው ሦስተኛው ክፍል ነው፡፡ በክፍል አንድ ምላሻችን የይሖዋ ምስክሮች የስሕተት ትምህርቶች ምን ምን እንደኾኑ፥ እንዲኹም መሠረታዊ የምሥጢረ ሥላሴን ትምህርት በመጠኑ ዐይተናል፡፡ በክፍል ኹለት ትምህርታችንም ከብሉይ እና ከሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት በማመሳከር ምሥጢረ ሥላሴ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርት እንደኾነ ተመልክተናል፡፡ ለዛሬ ደግሞ እግዚአብሔር በረዳን መጠን ከሐዋርያነ አበው ዠምረን እስከ ሦስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበሩ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ምን ብለው እንዳስተማሩ እንመለከታለን፡፡ ይኽን የምናደርግበት ምክንያትም የይሖዋ ምስክሮች የሥላሴ ትምህርት የተወሰነው በ325 ዓ.ም. በጉባኤ ኒቅያ በንጉሥ ቈስጠንጢኖስ አስገዳጅነት ነው ስለሚሉ ነው፡፡ እግዚአብሔር ዓይነ ልቡናችንን ያብራልን አሜን!!!

Wednesday, November 5, 2014

አምስቱ ስጦታዎች

በቀሲስ ፋሲል ታደሰ




(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ጥቅምት 27 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!! 

ሥርዓተ አምልኮ ከሚገለጥበት መንገድ አንዱ ስጦታ ነው፡፡ የሰው ልጅ ከራሱ የኾነ አንዳች የለውም፤ በጎ የኾነው ኹሉ ከፈጣሬ ዓለማት ከእግዚአብሔር ያገኘው ነው፡፡ በመኾኑም ፈጣሪያችን መስጠትን እንዳስተማረን ኹሉ እኛም ተገዥነታችንን ከምንገልጥበት አንዱ ከርሱ የተቀበልነውን በፈቃደኝነት በደስታ በመስጠት ነው፡፡ ነቢዩ ዳዊት ይኽን ሲያስረዳ “ኹ ከአንተ ዘንድ ነውና፡ ከእጅህ የተቀበልነውን ሰጥተንሃልና ይኽን ያኽል ልናቀርብልህ የቻልን ማነን? በፈቃዴ ይህን አቅርቤአለሁበማለት ከእግዚአብሔር ያገኘውን ሀብት በደስታ በፈቃዱ ለቤተ መቅደስ ሥራ እንዲውል መስጠቱን በመግለጽ ስለ ስጦታ ጽፏል /1ዜና 29÷9-16/፡፡

FeedBurner FeedCount