Wednesday, December 31, 2014

“ነገር ኹሉ ለበጐ እንዲደረግ እናውቃለን” /ሮሜ.8፡28/

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐሙስ ታኅሳስ 23 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
  አንዳንዴ በሕይወታችን ምንም የማይጠቅሙ ነገሮችን ልንመርጥ እንችላለን፡፡ የሚያስፈልገንና የሚጠቅመን ግን መንፈስ ቅዱስ ሲመርጥልን ነው፡፡ አደጋና ስጋት፣ በሽታና ስቃይ፣ እጦትና ችግር፣ ራብና ጥማት፣ ኀዘንና ትካዜ የሌለው ሕይወት እጅግ ጠቃሚ እንደኾነ አድርገን እናስባለን፡፡ ነገር ግን ይኽ የሌለው ሕይወት ኹሉ ጠቃሚም ላይኾን ይችላል፡፡
  እስኪ የሐዋርያው የቅዱስ ጳውሎስን ሕይወት እንደ ምሳሌ አንሥተን እንመልከተው፡፡ እግዚአብሔር በሰጠው ሀብተ ፈውስ የዕውራንን ዐይን የሚያበራው፣ የለምጻሞችን ለምጽ የሚያነጻው፣ ሙታንን የሚያነሣው፣ ሌላ ይኽን የመሰለ ተአምራትን የሚያደርግ ታላቁ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ሥጋውን የሚጐስም የሰይጣን መልእክተኛ ነበረው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ የሰይጣን መልእክተኛ ያለው አባቶች በሦስት መንገድ ይተረጕሙታል፡፡ ሰይጣን ማለት ጠላት፣ ክፉ፣ ተቃዋሚ ማለት ነውና /1ኛ ነገ.5፡4/ ቅዱስ ጳውሎስ የሰይጣን መልእክተኛ ተሰጠኝ ሲል፡-

Tuesday, December 30, 2014

ለይሖዋ ምስክሮች ኑፋቄ የተሰጠ ምላሽ (ክፍል አራት)



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ማግሰኞ ታኅሳስ 21 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

የሥላሴ ትምህርት በጕባኤ ኒቅያ አበው
 ውድ የመቅረዝ ተከታታዮች እንደምን ሰነበታችኁ? በጥያቄና መልስ ዓምዳችን ለይሖዋ ምስክሮች የስሕተት ትምህርት ኦርቶዶክሳዊ ምላሽ መስጠት ከዠመርን የዛሬው አራተኛው ክፍል ነው፡፡ በክፍል አንድ ምላሻችን የይሖዋ ምስክሮች የስሕተት ትምህርቶች ምን ምን እንደኾኑ፥ እንዲኹም መሠረታዊ የምሥጢረ ሥላሴን ትምህርት በመጠኑ ዐይተናል፡፡ በክፍል ኹለት ክፍለ ጊዜአችንም ከብሉይ እና ከሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት በማመሳከር ምሥጢረ ሥላሴ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርት እንደኾነ ተመልክተናል፡፡ በክፍል ሦስትም ከሐዋርያነ አበው ዠምረን እስከ ሦስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበሩ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ምን ብለው እንዳስተማሩ ተመልክተናል፡፡ ስለ ቅድስት ሥላሴ የመጨረሻው ክፍል በኾነው በዛሬው ምላሻችን ደግሞ በአጠቃላይ በጕባኤ ኒቅያ የነበረውን ሒደትና ውሳኔ እንመለከታለን፡፡ ይኽን የምናደርግበት ምክንያትም በክፍል ሦስት ምላሻችን እንደነገርናችኁ የይሖዋ ምስክሮች የሥላሴ ትምህርት የተወሰነው በ325 ዓ.ም. በጉባኤ ኒቅያ በንጉሥ ቈስጠንጢኖስ አስገዳጅነት ነው ስለሚሉ ነው፡፡ እግዚአብሔር ዓይነ ልቡናችንን ያብራልን አሜን!!!

Saturday, December 27, 2014

ነገረ መላእክት (Angelology)



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ቅዳሜ ታኅሳስ 18 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ትርጕም
 ጥሬ ቃሉን ስንመለከተው መልአክ የሚለው የግእዝ ቃል ኹለት ትርጉሞች አሉት፡፡ አንደኛው አለቃ፣ ሹም ማለት ነው፡፡ በዮሐንስ ራዕይ ላይ የምናገኛው ሰባቱ የቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪዎች መላእክት ተብለው መጠራታቸውም ከዚኽ አንጻር ነው /ራዕ. 2 እና 3/፡፡ ኹለተኛውና ከተነሣንበት ርእስ አንጻር ስናየው ደግሞ መልክእተኛ፣ የተሰደደ፣ የተላከ የሚል ትርጕም አለው /ዕብ.1፡14/፡፡ ይኸውም የመላእክት ተግባር ምን እንደኾነ የሚያስረዳ ቃል ነው፡፡ መላእክት ከእግዚአብሔር ወደ ሰው፥ ከሰውም ወደ እግዚአብሔር የሚላላኩ መናፍስት ናቸውና፡፡ መላእክት በሌላ ስማቸው የሰማይ ሠራዊት ተብለው ይጠራሉ፡፡

Thursday, December 25, 2014

ወደ እግዚአብሔር ለመድረስ (ደረጃ ሦስት)



በዲ/ን ሳምሶን ወርቁ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐሙስ ታኅሳስ 16 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!


“እንደ እንግዳ መኖር”
 የተከበራችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች የመንግሥተ እግዚአብሔር ተጓዦች እንዴት ሰነበታችሁ? እነሆ ሦስተኛውን የመንፈሳዊ ሕይወት ደረጃ በምናባችን ዛሬ እንመለከታለን፡፡ አስቀድመን የመጀመሪያውን የመንፈሳዊ ሕይወት ደረጃ ጀርባችንን ለዓለም በመስጠት ጀምረናል፡፡ በመንገዱ ያሰበበት ለመድስ የሚጓዝ አሽከርካሪ በመንገድ እንዳይቀር በየደረሰበት ከተማ ነዳጅ እንደሚሞላ እኛም ተስፋ ወደምናደርጋት መንግሥተ እግዚአብሔር እስክንደርስ ድረስ በየደረጃዎቹ ላይ የምናገኛቸውን የቃለ እግዚአብሔር ስንቅ እየቋጠርን እንጓዛለን፡፡ በባለፈው ጽሑፍ “ከዓለማዊ መሻት መለየት” ሁለተኛውን የመንፈሳዊ ሕይወት ደረጃ ተመልክተናል፡፡ ከዓለማዊ መሻት መለየት በዓለም ካለው አላፊ ጠፊ ከሆነው ከገንዘብ ከሥልጣን ከዕውቀት ፍቅር ተለይተን፤ በምድር ላይ ስንኖር አለን የምንለው ነገር ሁሉ ከእኛ እንዳልሆነ አውቀን፤ ከራስ ወዳድነት ርቀንና ከውዳሴ ከንቱ ተለይተን መኖር ማለት መሆኑን ተመልክተናል፡፡

Tuesday, December 23, 2014

ትምህርተ ሃይማኖት (ክፍል ስድስት)



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ማግሰኞ ታኅሳስ 14 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!


መ) ዶግማ እና ቀኖና
 ውድ የመቅረዝ ተከታታዮች! እንዴት አላችኁ? ትምህርተ ሃይማኖት በሚል ርእስ መማማር ከዠመርን የዛሬ ስድስተኛው ክፍል ነው፡፡ ባለፉት አምስት ተከታታይ ትምህርቶች የሃይማኖት ትርጕም፣ ሃይማኖት ያላቸው ፍጥረታት፣ የሃይማኖት አስፈላጊነት፣ ኦርቶዶክስና ተዋሕዶ ስለሚሉ አገላለጾች፣ ስለ ነገረ ቤተ ክርስቲያን፣ ስለ ቅዱስ ትውፊት እንዲኹም ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ኦርቶዶክሳዊ አረዳድ ተመልክተናል፡፡ ለዛሬ ደግሞ ከመግቢያው የመጨረሻ ስለኾነው ስለ ዶግማና ቀኖና እንማማራለን፡፡ ቢቻላችኁ ለማንበብ በቂ ጊዜ ሰጥታችኁና ተረጋግታችኁ ብታነቡት መልካም ነው፡፡ እግዚአብሔር ዓይነ ልቡናችንን ያብራልን፡፡ አሜን!!!

Friday, December 19, 2014

የንስሐ ልጆቼን እንዴት ላገልግል? (የመጨረሻው ክፍል)

በዳዊት አብርሃም
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ቅዳሜ ታኅሳስ 11 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
የጽሑፉ ምንጭ፡- ሐመር መጽሔት፥ የግንቦት 2005 ዓ.ም. እትም ነው፡፡
ኃጢአትን በመናዘዝ ውስጥ የሚገኝ ፈውስ
ከኃጢአት እስራት በንስሐ ለመፈታት ፈልጐ ወደ ካህኑ የሚቀርብ ተነሳሒ የሚታይበትና ከዚያም በሒደት አልፎበት በመጨረሻ የሚደርስበት የመንፈስና የሥነ ልቡና ኹኔታ አለ፡፡ ይኽንን ኹኔታ ቀሲስ ፋሲል ታደሰ እንደሚከተለው ይገልፁታል፡፡
ደረጃ አንድ
ተነሳሒው ለመዠመሪያ ጊዜ ሲመጣ የተረበሸ ኹኔታ ፊቱ ላይ ይነበባል፡፡ ቁጣ ቁጣ የሚለው የዘለፋና ወቀሳ የሚያበዛ ለራሱ የሰጠውን ዝቅተኛ ግምትና ውስጡ ያደረውን ታላቅ ተስፋ መቁረጥ ቁልጭ አድርገው የሚያሳዩ ኹኔታዎች ከገጽታው ይነበባል፤ ካንደበቱ ይደመጣል፡፡

Wednesday, December 17, 2014

የንስሐ ልጆቼን እንዴት ላገልግል? (4)

በዳዊት አብርሃም
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐሙስ ታኅሳስ 9 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
የጽሑፉ ምንጭ፡- ሐመር መጽሔት፥ የግንቦት 2005 ዓ.ም. እትም ነው፡፡
መንፈሳዊ ቤተ ሰብ
ቀሲስ ጥላኹን ታደሰ 110 ያኽል የንስሐ ልጆቻቸውን በጥንቃቄ መዝግበው ይዘዋል፡፡ ይኽም እያንዳንዱ የንስሐ ልጅ ያለበትን ደረጃ ለመከታተል አስችሏዋቸዋል፡፡ ከመዠመሪያው የንስሐ ልጆቻቸውን ለመቀበል መንፈሳዊ መስፈርቶችን በቅድመ ኹኔታነት ያስቀምጣሉ፡፡ በመዠመሪያ ግን የሚያቀርቡት ጥያቄ “ለምን የንስሐ አባት አስፈለገህ?” የሚል ነው፡፡ ይኽን ጥያቄ የሚያነሡት እያንዳንዱ የንስሐ ልጅ ትክክለኛውን ዓላማ ይዞ የንስሐ ሕይወቱን እንዲዠምር ለማድረግ ነው፡፡ ቀጥለው መስፈርቶቹን ይነግሩታል፡፡ ተስማምቶ ቢቀጥል እንኳ በየጊዜው ለመፈጸም የተስማማባቸውን መስፈርቶች በትክክል እየፈጸመ መኾኑን ከመመርመር አያቆሙም፡፡

Monday, December 15, 2014

የንስሐ ልጆቼን እንዴት ላገልግል? (3)

በዳዊት አብርሃም
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ማግሰኞ ታኅሳስ 7 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
የጽሑፉ ምንጭ፡- ሐመር መጽሔት፥ የግንቦት 2005 ዓ.ም. እትም ነው፡፡
ወጣቶችን ለንስሐ መጥራት
ለንስሐ አባትና ልጅ ግንኙነት እንደ አንድ ተግዳሮት እየኾነ ያለው ነገር የትውልድ ክፍተትና የባሕል ልዩነት ነው፡፡ በተለይ በከተሞች ውስጥ የሚኖሩ ወጣቶችን ዘመን አመጣሽ ችግሮች ተገንዝቦ መፍትሔ መስጠት በዕድሜ ከፍ ላሉትና ከገጠሩ አከባቢ ለመጡት ካህናት አስቸጋሪ ነው፡፡
 ቀሲስ ፋሲል ታደሰ ሌሎች ችግሮችንም ያወሳሉ፡- “የንስሐ ልጆች ከአባቶች ጋር ተገናኝተው ለመወያየት አመቺ ቦታም የሚጠፋበት ጊዜ አለ፡፡ ብዙ ጊዜ ቤተ ክርስቲያን አፀድ ስር እየተገናኘን ለመነጋገር ብንሞክርም በጕባኤ ሰዓት ወይም በሌሎች የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ሰዓት መወያየት ከባድ ይኾናል፡፡”
 ለዚኽ ችግር እንደ መፍትሔ ቢኾን ብለው ቀሲስ ፋሲል አንዲት ቢሮ ከፍተዋል፡፡ አራዳ ጊዮርጊስ አከባቢ የምትገኘው ቢሯቸው (በአኹኑ ሰዓት 5 ኪሎ በማኅበረ ቅዱሳን ሕንፃ ውስጥ ነው) በመጠን አነስተኛ ብትኾንም በውስጧ በርካታ መጻሕፍትን የያዘች ናት፡፡ ቀሲስ ስለዚኽ ነገር ሲያስረዱ፡- “ተነሳሕያኑ ምክር ከተቀበሉ በኋላ ስለ ሃይማኖታቸውም ኾነ ስለ ግል መንፈሳዊ ሕይወታቸው ዕውቀታቸው እንዲዳብር የተመረጡ መጻሕፍትን አውሳቸዋለኹ፡፡ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ግን የንባብ ፍቅር ስለሚያድርባቸው ራሳቸው እየገዙ ማንበብ ይዠምራሉ፤ እንዲያውም ለእኛ ያመጡልናል” ይላሉ፡፡

Wednesday, December 10, 2014

የንስሐ ልጆቼን እንዴት ላገልግል? (2)

በዳዊት አብርሃም
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐሙስ ታኅሳስ 2 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
የጽሑፉ ምንጭ፡- ሐመር መጽሔት፥ የግንቦት 2005 ዓ.ም. እትም ነው፡፡
የንስሐ ልጆች ጕባኤ
 አኹን አኹን የንስሐ ልጆቻቸውን መንፈሳዊ ፍላጐት ለማሟላት ጕዳይ እያሳሰባቸው የመጡ ካህናት የንስሐ ልጆቻቸውን የሚያሳትፍ ወርሐዊ ጕባኤ ያዘጋጃሉ፡፡ ቀሲስ አንተነህ ጌጡ ከእነዚኽ ካህናት አንዱ ናቸው፡፡ ቀሲስ አንተነህ በማኅበረ ቅዱሳን የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያ ፕሮግራም የትግበራ ቡድን አስተባባሪ ሲኾኑ በመደበኛ አገልግሎታቸው ተይዘው ዋነኛ የክህነት ተግባራቸውን ከፍጻሜ ሳያደርሱ እንዳይቀሩ በማለት 94 ለሚኾኑት የንስሐ ልጆቻቸው በማኅበረ ቅዱሳን ሕንፃ ላይ ወርኃዊ ጕባኤ ማዘጋጀት ከዠመሩ ሦስት ዓመት ሞላቸው፡፡ አዠማመሩን ሲገልጹ “የንስሐ ልጆቼ ጥቂት በነበሩ ጊዜ መገናኘት ቀላል ነበር፡፡ እየበዙ ሲሔዱ ግን አንድ በአንድ ዘወትር ማግኘት ይቸግራል፡፡ በዚኽ ጊዜ ደግሞ የንስሐ ልጆች መንፈሳዊ ሕይወት እንዳይጐዳ ለማድረግ በግለሰብ ደረጃ ያለውን ግንኙነት እንደ አስፈላጊነቱ በቀጠሮ እያደረጉ ኹሉን ደግሞ በቋሚ መርሐ ግብር በየወሩ በሚሠራ ጕባኤ ማከናወን ጥሩ አማራጭ ኾኖ ተሰማኝ፡፡”

Monday, December 8, 2014

የንስሐ ልጆቼን እንዴት ላገልግል? (1)

በዳዊት አብርሃም
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ማግሰኞ ኅዳር 30 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
የጽሑፉ ምንጭ፡- ሐመር መጽሔት፥ የግንቦት 2005 ዓ.ም. እትም ነው፡፡
 የንስሐ አባቶችን ሚና የሚያወሱና አገልግሎታቸውን የሚዘረዝሩ የሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት በተለይ ካህናት ምእመናንን የመጠበቅ የእረኝነት ተግባራቸው ላይ ያተኩራሉ፡፡ ካህናት ምእመናንን ቃለ እግዚአብሔር መመገብ አለባቸው፤ ይኸውም በአደባባይ መስበክን የሚመለከት ሲኾን ከዚኹም ጋር በግል ለእያንዳንዱ የንስሐ ልጃቸው ምክር አዘል የኾነ ቃለ እግዚአብሔርን ማካፈልን ይጨምራል፡፡

Thursday, December 4, 2014

ወደ እግዚአብሔር ለመድረስ (ደረጃ ሁለት)



በዲ/ን ሳምሶን ወርቁ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐሙስ ኅዳር 25 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ከዓለማዊ መሻት መለየት
 የተከበራችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እንዴት ሰነበታችሁ? ወደ እግዚአብሔር ለመድረስ በሚለው ጽሁፍ ወደ እግዚአብሔር ለመድረስ  በያዕቆብ ምናባዊ መሰላል ደረጃ ለዓለም ጀርባ መስጠት የመጀመሪያ መሆኑን ተመልክተናል፡፡ በዚህ ያዕቆብ በራዕይ በተመለከተው ምናባዊ መሰላል ላይ እግራችን መውጣት ጀምሯል፡፡ አሁን ለዓለም ጀርባ ስለሰጠን አይኖቻቸን ወደ እግዚአብሔር የሚመለከቱ ጆሮዎቻችን ድምጹን ለመስማት የሚቀኑ መሆን ይጀምራሉ፡፡ ምንያቱም ለዓለም ጀርባ ስለሰጠን ኃጢአትን መጥላት፣ የእግዚአብሔርን ፍቅሩንና ቸርነቱን መረዳት ጀምረናል፡፡ አሁን በእውነት እኛ ወደ እግዚአብሔር በማደርገው ጉዞ እንደርስ ይሆን የሚል ስጋት አይገባንም ምክንያቱም እኛ እስከፈቀድን ድረስ ከድካማችን ሊያሳርፈን ከወደቅንበት የሚያነሳን አምላክ ሊረዳን እንደቀረበ አውቀን ተረድተናልና፡፡ አሁን ጥያቄው እንዴት በመንገዳችን ጸንተን እንጓዝ የሚል ነው?

Tuesday, December 2, 2014

ስለ እመቤታችን ልደት (ለሕፃናትና ዠማሪዎች)



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ማግሰኞ ኅዳር 23 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!


ውድ የእግዚአብሔር ልጆች እንዴት ሰነበታችኁ? እግዚአብሔር ይመስገን ደኅና ነን አላችኁ? አሜን፡፡ እኔም በጣም ደኅና ነኝ እግዚአብሔር ይመስገን፡፡
 ልጆች! ባለፈው ጊዜ ስለምን እንደተማማርን ታስታውሳላችኁ? አቤል እና ቃየን ስለሚባሉ ኹለት ወንድማማቾች አይደል? ጐበዞች! ትክክል ናችኁ፡፡ ዛሬ ደግሞ ኹላችንም ስለምንወዳት ስለ እናታችን ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም ልደት እነግራችኋለኹ፡፡ ለመስማት ዝግጁ ናችኁ አይደል? ጐበዞች፡፡ እግዚአብሔር ዕውቀቱን ይግለጥልን፡፡ አሜን!!!

FeedBurner FeedCount