Friday, May 29, 2015

አንዲት/አሐቲ/ ሰንበት ትምህርት ቤት



በዲ/ን ሕሊና በለጠ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ግንቦት 21 ቀን 2007 ዓ.ም.)፡-  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
አንድወይምአንዲትየሚለው ቃል በቤተ ክርስቲያናችን ከቁጥር መግለጫነቱ ባሻገር የጠለቀ ምሥጢራዊ ፍች ያለው ቃል ነው፡፡
ከምሥጢራት ሁሉ የረቀቀውን የሥላሴን ምሥጢር አባቶች ባስተማሩንና በተገለጠልን መጠን ስንገልጽ አንድምሦስትም መሆናቸውን እንመሰክራለን፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ የምናመልከው አምላክ በባሕሪየ መለኮቱ አንድ እንደሆነ መጽሐፍ ቅዱስአንድ ጌታበማለት ይጠቁመናል፡፡ በእርሷ መንገድነት ካልሆነ በቀር ጌታን ማግኘት አይቻልምና ይሄ አንድ ጌታ የሚገኝባትን ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስትና ሃይማኖትን መጽሐፍ ቅዱስአንድ ሃይማኖትሲል ይጠራታል፡፡ ያመነና የተጠመቀ ነውና የሚድነው /ማር.1616/ የድኅነት መንገድ ወደሆነችው ወደዚህች ሃይማኖት መግቢያ በር የሆነውን ምሥጢረ ጥምቀትንም በመቀጠልአንዲት ጥምቀትሲል ይገልጸዋል፡፡/ኤፌ.45/ ሐዋርያት ልቡናቸውና ቃላቸው በአንድነት የተባበረ ነውና በኤፌሶን መልእክቱ ቅዱስ ጳውሎስአንድያላትን ሃይማኖት ሐዋርያው ይሁዳምለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽማ የተሰጠችይላታል፡፡ /ይሁ. 3/

Wednesday, May 27, 2015

መቅረዝ ዘተዋሕዶ: በዓለ ጰራቅሊጦስ

መቅረዝ ዘተዋሕዶ: በዓለ ጰራቅሊጦስ: (መቅረዝ ዘተዋሕዶ፥ ግንቦት ፴ ቀን፥ ፳፻፮ ዓ.ም)፡ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!     “ጰራቅሊጦስ” ማለት በጽርዕ ልሳን “አጽናኝ” ማለት ነው፡፡ ምንም እንኳን በ፩ኛ ዮሐ.፪...

Sunday, May 24, 2015

አልማዝ - መድሎተ ጽድቅ



በዲ/ን ብርሃኑ አድማስ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
      “መድሎተ ጽድቅ - የእውነት ሚዛን” በሚል ርእስ ዲ/ን ያረጋል አበጋዝ ያዘጋጀው መጽሐፍ ግንቦት 8 ቀን 2007 ዓ.ም. ብጹዕ አቡነ ሉቃስ የሰቲት ሑመራ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ አበው ካህናት፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ ሰባክያነ ወንጌል እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ደማቅ መርሐ ግብር መመረቁ ይታወሳል፡፡ በዕለቱም ዲ/ን ብርሃኑ አድማስ የመጽሐፉን ዳሰሳ አቅርቦ ነበር፡፡ ዳሰሳው ካለው ዘርፈ ብዙ ጥቅም አንጻር እንደሚከተለው አቅርቤዋለሁ፡፡ መልካም ንባብ!!!

Wednesday, May 20, 2015

መቅረዝ ዘተዋሕዶ: ዕርገተ ክርስቶስ

መቅረዝ ዘተዋሕዶ: ዕርገተ ክርስቶስ: (መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ግንቦት ፳ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!! ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ከተነሣ በኋላ ዕለቱን ወደ ሰማይ አላ...

Monday, May 18, 2015

ይድረስ ለሯጩ ወንድሜ

በአሃ ገብርኤል
ከዓምደ ሃይማኖት /ሰ/ት/ቤት
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ግንቦት 11 ቀን 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
        ይድረስ ለወንድሜ ተስፋ እግዚአብሔር! እንደምን ሰንብተኻል? እኔ ቸሩ እግዚአብሔር ይመስገን ደኅና ነኝ፡፡ “በተመረቅኩት ሥራ ብዙ ዓመታት መሥራቴን ታውቃለኅ፡፡ አኹን ግን ትቼው አትሌት ኾኛለኁ፡፡ ለመኾኑ ሯጭነት ኃጢአት ነውን?” ብለኽ የጻፍክልኝ ደብዳቤ ደርሶኛል፡፡
        ውድ ወንድሜ! ሩጫችን ይለያያል እንጂ ኹላችንም ሯጮች ነን፡፡ በርግጥ የሚገባና የማይገባ ሩጫ እንዳለ ልትዘነጋ አይገባም፡፡ ጥያቄኽ የኹላችንም ጥያቄ በመኾኑ የጥያቄአችን መልስ የሚኾነን ደግሞ ቃለ እግዚአብሔር ነው፡፡ ታስታውስ እንደኾነ የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት ከኾንን በኋላ በጕባኤ “ታገኙ ዘንድ ሩጡ” /1ኛ ቆሮ.9፡24/ በሚል ርእስ ተምረን ነበር፡፡ ዛሬ አንተ ሯጭ ኾነህ በምሳሌ የተማርነውን በተግባር እያስታወስከው እንድትማርበት ዕድሉን በማግኘትህ ደስ ልትሰኝ ይገባኻል፡፡

Thursday, May 14, 2015

በፊቴም እረዱአቸው /ሉቃ.19፡27/



በዲ/ን ዶ/ር ቴዎድሮስ በለጠ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ግንቦት 6 ቀን 2007 ዓ.ም.)፡-  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ስመ እግዚአብሔር ቀዳማዊ ዘእንበለ ትማልም፤ ወማዕከላዊ ዘእንበለ ዮም፤ ወደኃራዊ ዘእንበለ ጌሰም ፤ብሉየ መዋዕል ዘእንበለ ዓም፤ ፈጣሬ ኩሉ ዓለም ዘእንበለ ድካም፤ ባህረ ምሕረት ዘእንበለ አቅም፤ ብኁተ ሕሉና እስከ ለዓለመ ዓለም አሜን::
"ወባህቱ ለእልክቱሰ ጸላእትየ እለ ኢይፈቅዱ እንግሥ ላእሌሆሙ አምጽእዎሙ ዝየ ወርግዝዎሙ በቅድሜየ= ነገር ግን እነዚያን በላያቸው ልነግሥ ያልወደዱትን ጠላቶቼን ወደዚህ አምጡአቸው ።" ሉቃ.19:27

Tuesday, May 12, 2015

“ከካህናት ጋር አብሬ ስለማገለግል ንስሐ መግባት ከበደኝ፡፡ ምን ላድርግ?”



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ማግሰኞ ግንቦት 4 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ውድ መቅረዛውያን እንዴት አላችኁ? ዛሬም ከአንባብያን ከተላኩልኝ ጥያቄዎች መካከል አንዱን መርጬ በአበው ካህናት የተሰጠውን ምላሽ ይዤላችኁ ቀርቢያለኁ፡፡ ዛሬም መልሱን የሚሰጡን በምሥራቀ ፀሐይ ቀበና መድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን ሰባኬ ወንጌል እንዲኹም በታዕካ ነገሥት ባዕታ ለማርያም ገዳም የመጻሕፍተ ሐዲሳት የ5ኛ ዓመት ደቀ መዝሙርና የዘንድሮ ተመራቂ የኾኑት ቀሲስ ፋሲል ታደሰ ናቸው፡፡ ለአባታችን ተናጋሪ አንደበት ለእኛም ሰሚ እዝነ ልቡና ያድለን፡፡ አሜን!!!
ጥያቄ፡-  “ውድ መቅረዞች! እንዴት አላችኁ? የመቅረዝ አንባቢ ነኝ፡፡ ከምእመናን የምታስተናግዱት ጥያቄ በጣም ጥሩ ነው፡፡ እኔም ከንስሐ አባት ጋር የተያያዘ ጥያቄ አለኝ፡፡ እኔ በምኖርበት አከባቢ ከካህናት ጋር አብሮ የመሥራትና የመቀራረብ ነገር አለ፡፡ ይኽም ለእኔ ብቻ ሳይኾን የሀገሩ ጠባይ የፈጠረው ነው፡፡ እናማ ባለን ቅርርብ በቤተ ክርስቲያን ጕዳይ አለመግባባት ሲፈጠርም ኾነ በሌላ ጕዳይ በአካልም ኾነ በስልክ እንደ ልብ ስለምናወራ የሰው ስም እያነሣን ስናማ፣ ስናወግዝ አብረን ስለምንውል እንዴት መናዘዝ እችላለኁ?”
አንዳርግ ነኝ ከቺካጎ

Saturday, May 2, 2015

ለክርስትና ሃይማኖት ግድ ያለው ሰው ኹሉ ሊያነበው የሚገባ መጽሐፍ!



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ 24 ቀን 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
በዲያቆን ያረጋል አበጋዝ የተዘጋጀውና “መድሎተ ጽድቅ (የእውነት ሚዛን)” የተሰኘው ድንቅ መጽሐፍ በገበያ ላይ ዋለ፡፡
ይኽ መጽሐፍ ራሳቸውን “ተሐድሶ” ብለው የሚጠሩት አካላት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን እምነትና ትምህርትን በተመለከተ በሐሰትና በስሕተት ላሠራጯቸው የስሕተት ትምህርቶች መልስ የሚሰጥ ድንቅ መጽሐፍ ሲኾን በአንጻሩም መጽሐፍ ቅዱሳዊና ሐዋርያዊ የኾነው የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ትምህርት በጥልቀትና በስፋት የቀረበበት መጽሐፍ ነው፡፡ በውስጡም፡-

FeedBurner FeedCount