Monday, June 22, 2015

ሒዱ እንጂ ተቀመጡ አልተባልንም (ክፍል ኹለት)



በዲ/ን ዳንኤል ክብረት
(መዝረቅ ዘተዋሕዶ፣ ሰኔ 16 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ኹለተኛው በይሁዳ ነው!
ይሁዳ የኢየሩሳሌም አውራጃው ነው፡፡ የይሁዳ አውራጃ ዋና ከተማም ኢየሩሳሌም ነች፡፡ ከኢየሩሳሌም ይሁዳ ይከፋል፤ ከሰማርያ ግን ይሻላል፡፡ ምክንያቱም ኢየሩሳሌም ዋና ከተማዋ ነች፣ ጌታም የተወለደው በይሁዳ አውራጃ በቤተ ልሔም ነው፡፡ የተሰቀለው፣ የሞተው፣ የተቀበረው፣ ያረገው፣ መንፈስ ቅዱስን ለሐዋርያት የላከው በኢየሩሳሌም ከተማ ነው፡፡ ስለዚህ የኢየሩሳሌም ነገር በይሁዳ አውራጃ የተሻለ ይወራል፤ ይነገራል፡፡ የሚያውቁት ዘመድ ይኖራል፡፡ የሐዋርያትና የይሁዳ ቋንቋ ተመሳሳይ ነው፡፡ የይሁዳ ባሕልና የኢየሩሳሌም ባሕል ተመሳሳይ ነው፡፡ ከሰማርያ ቢሻልም ከኢየሩሳሌም ግን ይከፋል፡፡

Tuesday, June 16, 2015

ሒዱ እንጂ ተቀመጡ አልተባልንም (ክፍል አንድ)



በዲ/ን ዳንኤል ክብረት
      (መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሰኔ 9 ቀን 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
     ውድ የመቅረዝ አንባብያን! እንዴት አላችሁ? ይህ ጽሑፍ ዲ/ን ዳንኤል ክብረት ማኅበረ ቅዱሳን ሰኔ 7 ቀን 2007 ዓ.ም. ወደ ቡኢ ደብረ ሰላም በዓለ ወልድ ቤተ ክርስቲያን ባዘጋጀው የበእንተ ወንጌል መርሐ ግብር ላይ ያስተማረው ትምህርት ነው፡፡ ስብከቱ አንድ ሰዓት ከዐሥር ደቂቃ የሚፈጅ ስለኾነ ወደ ጽሑፍ ሲቀየር ትንሽ በዛ ይላል፡፡ በመኾኑም በኹለት ክፍል እንዳቀርበው ተገድጃለሁ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ዲ/ን ዳንኤል ሲሰብክም የሚያነብ ስለሚመስል ብዙ የሚደጋገሙ ዐረፍተ ነገሮችን ስለሌሉበት፥ ያስተካከልኩት ነገር ቢኖር በጉባኤው ላልነበረ ሰው የማይረዱ ጥቃቅን ስንኞችን ብቻ ነው፡፡ ስለ ኹሉም መልካም መልካም ንባብ ይኹንላችሁ!!!

Thursday, June 11, 2015

መልከኞቹ



በደቀ መዝሙር ተስፋሁን ነጋሽ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሰኔ 4 ቀን 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
አንዲት ባለጠጋ እናት አሉ፡፡ ታዲያ ቀደም ሲል ካከበርናቸው ዐበይት በዓላተ እግዚእ መካከል አንዱ የሆነውን በዓለ ጰራቅሊጦስ አብሬአቸው እንዳሳልፍ በክብር ጋብዘውኝ ከቤታቸው ተገኘሁ፡፡ እኒያ እናት ሦስት ልጆች ያላቸው ሲሆን የልጆቹ ውበት ልዩ ነው፡፡ እንዲያውም አንድ ወዳጄ የልጆቹን መልክ ዓይቶ ‹‹በሥላሴ አምሳል የተፈጠሩትስ እኒህ ልጆች ናቸው›› ሲለኝ በፈገግታ ማለፌን አልዘነጋውም፡፡ አንዱን አይታችሁ ወደ ሌላኛው ስትዞሩ የባሰ እንጂ ያነሰ ቁንጅና አታዩም፡፡ በመሆኑም ወደዚያ ቤት የገቡ እንግዶች ሁሉ ስለ ልጆቻቸው ቁንጅና ሳይናገሩ አይወጡም፡፡ ስለ ትልቁ ልጃቸው ግርማ ሞገስ፣ ስለ ተከታይዋ ሸንቃጣነት፣ ስለ ትንሹ ልጃቸው ቅላት አንዱ ከሌላው አፍ እየነጠቀ የልቡን አድናቆት ይገልጣል፡፡ እናት ስለ ልጆቻቸው የሚባለውን ሁሉ ከሰሙ በኋላ ግን ‹‹ልክ ናችሁ ልጆቼ መልክኞች ናቸው፤ ግን ኃይለኞች አይደሉም›› ይላሉ፡፡ ይህ ንግግራቸው እኔን ግራ ስላጋባኝ ‹‹ምን ማለትዎ ነው? አሁን እነዚህ ልጆች ምን ይወጣላቸዋል?›› በሚል የአድናቂነት ወግ ጠየቅኋቸው፡፡ እርሳቸውም ‹‹መልሱ ያለው ሁለተኛ ጢሞቴዎስ ላይ ነው›› አሉኝና ‹‹የአምልኮት መልክ አላቸው ኃይሉን ግን ክደዋል፤ ከእነዚህ ደግሞ ራቅ›› የሚለውን ቅዱስ ቃል አነበቡልኝ፡፡ /2ኛ ጢሞ. 3፤5/

Monday, June 8, 2015

ትምህርተ ሃይማኖት (ክፍል ዐሥራ አንድ)

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሰኔ 2 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
የእሑድ ዕለት ፍጥረታት
የእሑድ ሰዓተ ሌሊት ፍጥረታት
እሑድ ማለት የዕለታት መጀመሪያ ማለት ሲኾን ይኸውም እግዚአብሔር ፍጥረቱን የፈጠረበት የመጀመሪያው ቀን ነው፡፡ በዚህ ዕለት ስምንት ፍጥረታት የተፈጠሩ ሲኾን፥ እነርሱም፡-
ü  በመጀመሪያ ሰዓተ ሌሊት - አራቱ ባሕርያተ ሥጋ እና ጨለማ፣
ü  ከኹለተኛው ሰዓተ ሌሊት እስከ ዘጠነኛው ሰዓተ ሌሊት - ከእሳት ሙቀቱን ትቶ ብርሃኑን ወስዶ ሰባቱ ሰማያትን፣
ü  በዘጠነኛው ሰዓተ ሌሊት ደግሞ መላእክትን ፈጠረ፡፡
እስኪ እያንዳንዳቸውን በመጠን በመጠኑ እንመልከታቸው፡፡

Monday, June 1, 2015

ትምህርተ ሃይማኖት (ክፍል አስር)

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ግንቦት 25 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ውድ የመቅረዝ አንባብያን! እንዴት ሰነበታችሁ? እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ዛሬም የትምህርተ ሃይማኖት ትምህርታችንን እንቀጥላለን፡፡ በዛሬው ክፍልም በክፍል ዘጠኝ የጀመርነውን የሥነ ፍጥረት ትምህርት ይኾናል፡፡ እግዚአብሔር ማስተዋሉን ጥበቡን ያድለን፡፡ አሜን!!!

FeedBurner FeedCount