Thursday, March 31, 2016

መጻጉዕ - ለምን እስከ ሠለሳ ስምንት ዓመት ሳይድን ቆየ?



በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 22 ቀን 2008 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ተወዳጆች ሆይ! እነሆ እግዚአብሔር ፈቃዱ ኾኖ በዚህ ሳምንትም “ወደ ኦሎምፒያስ የተላኩ መልእክታት እና ሌሎች” በተሰኘ አዲስ የሊቁ መጽሐፍ ተገናኝተናል፡፡ እርሱ እስከ ወደደ ድረስም እስከ አሁን በተተረጎሙት ሳንረካ ብዙ ለመተርጎም ወደ ፊት እንሔዳለን፡፡ የሊቁ ሥራዎች ለዚህ ትውልድ ዓይነተኛ መድኃኒቶች ናቸውና፤ እንዲሁ ለማወቅ ያኽል ብቻ ተነብበው በመጻሕፍት መደርደሪያ ላይ የሚቀመጡ ሳይኾኑ መንፈሳዊ ሕይወታችን እንዲጎለምስ ዕለት ዕለት ልናነባቸው የሚገቡ ናቸውና፤ በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ላይ እስከ ምን ድረስ ጠንካራ ክርስቲያኖች ልንኾን እንደሚገባን የሚያሳዩ ናቸውና፡፡
ሊቁ፥ በዚህ መጽሐፍ ላይ ሦስት ዋና ዋና ርእሶችን ይዞልን ቀርቧል፡፡ በመጀመሪያው ርእስ ላይ የእግዚአብሔር ከአእምሮ የሚያልፍ አሠራርና ፍቅር፥ ጓደኞቹ የቤቱን ጣራ ነድለው ባወረዱት ሽባ አንጻር እናያለን፡፡ እንዲሁ የበይ ተመልካቾች ግን አንኾንም፤ የድርሻችንን ዘግነን እንወስዳለን እንጂ፡፡ በኹለተኛው ዐቢይ ርእስ “ሰው ራሱን ካልጎዳ በስተቀር ማንም እርሱን ሊጎዳው እንደማይችል” በማለት የሰው ብቸኛና እውነተኛ ጠላቱ እርሱ ራሱ እንደ ኾነ ያስረዳናል፤ ማስረዳት ብቻም ሳይኾን መፍትሔዉንም ያመላክተናል፡፡ በሦስተኛው ዋናው ርእስ ላይ ወደ አምስት የሚኾኑ ንኡሳን አርእስት አሉ፡፡ እጅግ በጣም አስደናቂ ወደኾነችው ወደ ዲያቆናዊት ኦሎምፒያስ የላካቸው መልእክታት ናቸው፡፡ በእነዚህ መልእክታት ውስጥ እጅግ በጣም ብዙ አሳቦች ተነሥተዋል፡፡ በዚህ ዘመን ያሉ ሊቃነ ጳጳሳት፣ ካህናትና አገልጋዮች ከእነዚህ የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ደብዳቤዎች እጅግ በጣም ብዙ ቁም ነገሮችን ያገኛሉ፡፡ ራሳቸውንና አገልግሎታቸውን ይመዝናሉ፡፡ ምእመናንም በአስደናቂዋ ሴት አንጻር ራሳችንን እንመለከታለን፡፡ አሻቅበን ማየት ከተቻለንም ከዲያቆናዊቷ ከኦሎምፒያስ ምን ያኽል ርቀት ላይ እንዳለን እናያለን፡፡ የዘመኑ ባለጸጎችም ከዚህች ባለጸጋ ሴት የድርሻችሁን ትወስዳላችሁ፡፡
አሁን እዚህ የማቀርብላችሁ ትምህርትም በቤተ ክርስቲያናችን ሥርዓት መሠረት ይህ ሳምንት “መጻጉዕ” እንደ መባሉ ሊቁ በዚህ መጽሐፍ ስለ መጻጉዕ ካስተላለፈልን ትምህርት የተቀነጨበ ነው፡፡ መልካም የምክርና የተግሣጽ ጊዜ ይኹንልዎት!

Tuesday, March 22, 2016

ማርታም ታገለግል ነበር


                                                በዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
(ከመጽሐፈ ገጹ የተወሰደ)
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 13 ቀን 2008 ..)- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ማርያምና ማርታ እኅትማማቾች ናቸው፡፡ኢየሱስም ማርታንና እኅትዋን አልዓዛርንም ይወድ ነበር› (ዮሐ. 115) ስለዚህም በቢታንያ በሚገኘው ቤታቸው እንግዳ ሆኖ ተገኘ፡፡ እጅግ ለሚወዱት ጌታ ፍቅራቸውን ለመግለጽ እኅትማማቾቹ ይሻላል ብለው ያሰቡትን ሁለት የተለያየ ዓይነት አቀባበል አድርገውለት ነበር፡፡ ማርታ ለምትወደው እንግዳዋ ምግብ ለማቅረብ ብዙ ተጨንቃ በጓዳ ሥራ ላይ ተወጠረች፡፡ለታላቁ ጌታ ምን ላቅርብለት ይሆን?› ብላ ተጠበበች፡፡ መቼም የምናከብረው ሰው እንግዳ ሆኖ ሲመጣ ሙያውም ሊጠፋብን ይችላል፡፡ ማርታም የገጠማት ይኼው ነው ምኑን ከምኑ አድርጋ እንደምታቀርብ ግራ ገባት ጌታችን እንዳለውበብዙ ነገር ተጨነቀች ታወከች፡፡

Saturday, March 12, 2016

መቅረዝ ዘተዋሕዶ : አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ

መቅረዝ ዘተዋሕዶ : አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ: (መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 03 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!      በየዓመቱ መጋቢት 5 የምናከብረው በዓል አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ያረ...

በዐቢይ ጾም ስድስተኛ ቀን ላይ የተሰጠ ተግሣጽ



በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 03 ቀን 2008 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ይህ ተግሣጽ ሊቁ የኦሪት ዘፍጥረትን መጽሐፍ እየተረጎመላቸው ሳለ በዐቢይ ጾም ስድስተኛው ቀን ላይ በዚያ ሰዓት እንደ ትልቅ መዝናኛ ይቈጠር የነበረውን የፈረስ ግልቢያን ለማየት ጉባኤዉን ትተው ለሔዱ ምእመናን የሰጠው ተግሣጽ ነው፤ ልክ የዛሬ 1620 ዓመት መኾኑ ነው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ይህን ተግሣጽ በእኛ ዘመን ኾኖ ቢያስተላልፈው ኖሮ እኛ እንደ ትልቅ መዝናኛ የምናያቸውን እንደ እግር ኳስ፣ ፊልም፣ እና የመሳሰሉትን ሊጠቀም እንደሚችል ምንም ጥርጥር የለውም፡፡ ለማንኛውም እስኪ እያንዳንዳችን ከያለንበት ኹናቴ እያየን ተግሣጹን ለእኔ ብለን እናድምጠው፡፡ አሁን ወደ ሊቁ፡- 
(1) ዛሬም እንደተለመደው ትምህርታችንን እንድንቀጥል እፈልጋለሁ፡፡ ነገር ግን እያመነታሁ ነው፡- ተስፋ የመቁረጥ ስሜት ከብቦኛል፤ ግራ ገብቶኛል፤ ውስጤ ታምሟል - ተስፋ መቁረጥ ብቻ አይደለም፤ እጅግ አዝኛለሁ፡፡ ምን ማድረግ እንዳለብኝ አላውቅም፤ የጥርጣሬ ስሜት ውስጤን ልምሾ አድርጎታል፡፡ ዕለት ዕለት ከዲያብሎስ ግብር ትርቁ ዘንድ ስናስተምራችሁና ስንመክራችሁ እንዳልነበረ፥ እናንተ ግን ወደዚያ ዲያብሎሳዊ ግብር ጥርግ ብላችሁ ሔዳችሁ፡፡ ከቃለ እግዚአብሔር ይልቅ የፈረስ ግልቢያው ማረካችሁ፡፡ እስከ አሁን ድረስ በማስተምራችሁ ትምህርት ለውጥ ካላመጣችሁ ከዚህ በላይ ላስተምራችሁ የምችለው ምን ብዬ ነው? ከምንም በላይ ተስፋ እንድቆርጥባችሁና ብስጭቴ ጣራ እንዲነካ ያደረገው ደግሞ ይኸን ኹሉ እየመከርናችሁ እየዘከርናችሁ ሳለ ዐቢይ ጾሙን መናቃችሁና ራሳችሁን በዲያብሎስ መረብ ውስጥ መጣላችሁ ነው፡፡ የፈለገ ያህል ልቡናው እንደ ድንጋይ ቢጠነክር እንዴት በዐቢይ ጾም ውስጥ ሰው እንደዚህ ያደርጋል? እመኑኝ! በጣም አፍሬባችኋለሁ፤ እስከ አሁን ድረስ ያስተማርኩት ትምህርት ምንም ጥቅም እንዳላስገኘ በማየቴና ጭንጫ ላይ ስዘራ በመክረሜ በጣም አፍሬባችኋለሁ፡፡

Sunday, March 6, 2016

የዐቢይ ጾምን መግባት ምክንያት በማድረግ የተሰጠ ትምህርት

በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 28 ቀን፣ 2008 ዓ.ም.)፤- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ይህ ትምህርት የተወሰደው የተወደደ መምህር ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ በ388 ዓ.ም. ዐቢይ ጾም መግቢያ ላይ ጀምሮት በቀጣዩ ዓመት ጥቅምት መጨረሻ ላይ እየተረጎመ ከጨረሰው የኦሪት ዘፍጥረት መጽሐፍ ነው፡፡ ይህን ትምህርት ይከታተሉ የነበሩትን ምእመናን ከሊቁ አጠቃላይ ንግግር አንጻር ስናያቸውም የቤት እመቤቶችና በተለያየ የሙያ ሥራ የተሰማሩ ሠራተኞች ሲኾኑ የሚማሩትም በዐቢይ ጾም ምንም እኽል ሳይቀምሱ ነው፡፡   
(1) የእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን እንደዚህ በልጆቿ ስትደምቅ እናንተም ጉባኤውን ለመታደም ደስ ብሏችሁ ተሰባስባችሁ ስትመጡ ዐይቼ ሐሴት አደረግሁኝ፤ ደስም አለኝ፡፡ ፊታችሁ እንዴት በደስታ እንደ ተመላ ስመለከት ጠቢቡልብ ደስ ሲለው ፊት ይበራልእንዳለው ልባችሁ ምን ያህል እንደ ተደሰተ ተገነዘብሁኝ /ምሳ.1513/፡፡ በመኾኑም፥ ዛሬ ማለዳ የተነሣሁት ከወትሮው በተለየ ትጋት ነው፡፡ ይኸውም ይህን መንፈሳዊ ደስታ ከእናንተ ጋር እንድካፈልና ቀጣዩ ወራት ቁስለ ነፍሳችሁ ድኅነት የሚያገኝበት ወርሐ መኾኑን አበሥራችሁ ዘንድ ነው፡፡ የኹላችንም ጌታ ልዑል እግዚአብሔር፥ ልክ እንደ ደግ አባት ባለፉት ወራት ለሠራነው ኃጢአት ሥርየት እናገኝበት ዘንድ ሽቶ መድኃኒት የሚኾን ቅዱስ ጾምን አዘጋጅቶልናልና፡፡

Thursday, March 3, 2016

“ሦስቱ የኃጢያት አለቆች” ማቴ ፬፥፩-፲፩



ዳዊት ተስፋይ
ከተክለ ሳዊሮስ ሰ/ት/ቤት
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 24 ቀን፣ 2008 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
        ኃጢያት ኃጥአ አጣ ከሚለው የግዕዝ ግስ የተገኘ ሲሆን ማጣት ማለት ነው፡፡አንድ ሰው ኃጢያትን ሲሰራ እግዚአብሔርን ፣ እናቱን ቅድስት ድንግል ማርያምን ፣ ቅዱሳኑንና ፣ የከበረች መንግስቱን ያጣልና ኃጢያት ማጣት የሚል ትርጉም ተሰጥቶታል፡፡ በዓለም ላይ ብዙ አይነት ኃጢያቶች ቢኖሩም እናታችን ቅድስት ቤ/ክ ኃጢያቶች ሁሉ ሦስት አለቆች እንዳሏቸው ታስተምራለች፡፡ እነዚህም ስስት ፣ ትዕቢትና ፍቅረ ነዋይ ናቸው፡፡ እነዚህ ኃጢያቶች ‹‹አለቆች›› መባላቸውም የሁሉም ኃጢያቶች መገኛ ስለሆኑና እነዚህን ሦስቱ ኃጢያቶች ድል ያደረገ ሌሎቹንም ኃጢያቶች ድል ያደርጋልና ነው፡፡ ለዛሬ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በገዳመ ቆሮንቶስ ‹‹ሦስቱን የኃጢያት አለቆች›› እንዴት ድል እንዳደረጋቸውና እኛም እንዴት ድል ልናደርጋቸው እንደምንችልና እንዲሁም ታሪኩ ለመንፈሳዊ ሕይወታችን ምን ትምህርት እንደምናገኝበት የቅዱሳን አባቶቻችንን ትርጓሜ መነሻ አድርገን በአጭሩ እንነጋነጋለን፡፡ ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ ታሪኩን እንዲህ እያለ መተረክ ይጀምራል፡- “ማቴ ፬፥፩ ከዚህ በኋላ ከዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ መንፈስ ጌታችንን ኢየሱስን ወደ ምድረ በዳ ወሰደው ፤ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጾመ ፤ ከዚህም በኋላ ተራበ ”፡፡

FeedBurner FeedCount