Monday, May 23, 2016

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ - ክፍል ፮ (የመጨረሻው)

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ግንቦት 15 ቀን፣ 2008 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
በዛ ቢልም በትዕሥት ኾነው ያንብቡት፡፡
ጉባኤ ኦአክ
በክፍል አምስት ለመግለጽ እንደተሞከረው ቴዎፍሎስ በቅዱስ ኤጲፋንዮስ አማካኝነት ሊያደርገው ያሰበው ነገር አልሰመረለትም፡፡ ነገር ግን በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ላይ እርሱ ራሱ ከሳሽና ዳኛ ለመኾን እጅግ ሲጨነቅና ሲጠበብ ቆይቷል፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ነገሮች እንደ ድሮ እንዳሉ በማሰብ ቅዱስ ኤጲፋንዮስ እንደ ወጣ ማለትም በዚህ በወርሐ ግንቦት አጋማሽ ላይ ስለ ሴቶች አለባበስ አስደናቂ የኾነ ስብከትን ሰበከ፡፡ አውዶክስያም ይህን ስብከት ሰማች፡፡ አንዳንድ ሰዎችም - በተለይ ሴቪሪያን የተባለ - ስብከቱ እርሷን ያነጣጠረ እንደ ኾነ ነገሯት፡፡ እጅግ ተናደደች፡፡ ይህንንም ይዞ ወደ አርቃድዮስ (ወደ ባለቤቷ) ሔደች፡፡እኔን ሰደበ ማለት አንተንም ሰደበ ማለት ነውአለችው፡፡ ብዙዎቹ የታሪክ ጸሐፊዎች የቅዱስ ዮሐንስና የአውዶክስያ ግንኙነት የሚሻክረው በዚህ ምክንያት ነው ይላሉ፡፡ 

Sunday, May 22, 2016

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ - ክፍል ፭


(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ግንቦት 14 ቀን፣ 2008 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ተዋዳጆች ሆይ! ክፍል አምስትን ሳላቀርብላችሁ ዘገየሁ፡፡ ይቅርታ ይደረግልኝ፡፡ ከዓቅሜ በላይ የኾነ ጉዳይ ገጥሞኝ ነው፡፡
ቁስጥንጥንያ ከተማ
እስኪ ስለ ቁስጥንጥንያ ጥቂት እንበል! ከአንጾኪያ ይልቅ ቁስጥንጥንያ ከቤተ ክርስቲያናዊም ኾነ ከፖለቲካዊ ፋይዳዋ ከፍ ያለ ነው፡፡ መሥራቿ ታላቁ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ነው፤ 330 ..፡፡ በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ዘመን ከአራት መቶ እስከ አምስት መቶ ሺሕ ኗሪ ነበራት፡፡ መንበረ ፓትሪያሪኩ ለቤተ መንግሥቱ በጣም ቅርብ ነው፤ ሃጊያ ሶፍያ (ቅድስት ጥበብ - መድኃኔ ዓለም በሉት፡፡ ጥበብ ክርስቶስ ነውና)፡፡ በከተማይቱ ሦስት አብያተ ክርስቲያናት ነበሩ፡- 381 .. ጉባኤ ቁስጥንጥንያ የተካሔደበትና ከሃጊያ ሶፍያ 150 ሜትር ገደማ የሚርቀው ሃጊያ ኢረነ (ቅድስት ሰላም) ወደ ምዕራብ አቅጣጫ የሚገኝ የቅዱሳን ሐዋርያት ቤተ ክርስቲያን እንዲሁም በዮሐንስ መጥምቅ ምትረተ ርእስ የተሰየመ ቤተ ክርስቲያን ናቸው፡፡ በቅዱሳን ስም ቤተ ክርስቲያንን መሰየም የቅርብ ዘመን ታሪክ እንዳልኾነ እያስተዋላችሁ ነውን?

Friday, May 20, 2016

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ - ክፍል ፬

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ግንቦት 12 ቀን፣ 2008 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

አባ ዮሐንስ አፈወርቅ

ከዚህ በፊት እንደገለጽነው ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ወደ ገዳም እንዳይሔድ የዘገየው በእናቱ ተማጽኖ ነው፡፡ 372 .. ግን እናቱ ስላረፈች ይጓጓለት ወደነበረው ገዳም ሔደ፡፡ የገዳሙ ስም ሲልፕዮስ ይባላል፡፡ ሲልፕዮስ እጅግ ጫካ የተሞላበት የጽሞና ሥፍራ ነው፡፡
ጰላድዮስ እንደሚነግረን ቅዱስ ዮሐንስ ወደዚህ እንደ ደረሰ አንድን አባት አገኘ፤ አባ ሲሲኮስ ይባላሉ፡፡ አራት ዓመትንም ከእርሳቸው ጋር ቆየ፡፡ በዚህ አራት ዓመት ውስጥ ከእኒህ አባት በዓት አጠገብ የራሱ የኾነ በዓት ነበረው፡፡ ሌሊቱን ሙሉ እንደዚሁም ከቀኑ አብዛኛውን ሰዓት በበዓቱ ያሳልፍ ነበር፡፡ አብዝቶ ይጸልያል፤ ቅዱሳት መጻሕፍትን ያነባል፡፡ በተለይ በዚህ ገዳም የጽሞና ሕይወት በእጅጉ ይተገበር ነበር፡፡ የሚተኛው በሳር በተጎዘጎዘ መሬት ላይ ነበር፡፡ የሚለብሰው የፍየልና የግመል ቆዳ ነው፡፡ የሚበላው በቀን አንዴ ሲኾን ዳቦ በጨው ነበር፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ይህ ኹልጊዜ ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገር የኾነው ሕይወት፡- “አዳም ከመበደሉ በፊት የነበረው ሕይወት ነውብሎ የማቴዎስ ወንጌልን ሲተረጉም 38ኛው ድርሳኑ ላይ ገልጾታል፡፡ አባ ሲሲኮስ ብዙ አምላካዊ ራዕዮችን እያዩ የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የወደፊት ታላቅነቱን ዐይተዋል፡፡

FeedBurner FeedCount