Wednesday, September 12, 2012

ዜና ሐዋርያት


 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
   መንደርደርያ ይሆነን ዘንድ እስከ አሁን ባቀረብናቸው ሁለት ክፍሎች (እነዚያን ለማንበብ ይህን ይጫኑ http://mekrez.blogspot.com/2012/08/blog-post_7538.html) ክርስቲያኖች ለባሴ ክርስቶስ (ክርስቶስን የለበሱ) ዘላለማዊ ሕይወትን የያዙ ማለት እንደሆኑና ቅዱሳን ደግሞ ዘላለማዊ በሆነ በክርስቶስ ከፍተኛ የቅድስና ደረጃ ላይ የደረሱ፣ ሞት የማይሠለጥንባቸው ፍጹማን ክርስቲያኖች፣ ሁለንተናዊ ሕይወታቸው በክርስቶስ የሆነ እንደሆኑ ተመልክተናል። ከዚህ በተጨማሪ እኛም እንደ እነርሱ እውነተኞች የተግባር ክርስቲያኖች ለመሆንና በክርስቶስ በሕይወት ለመኖር የቅዱሳንን ሕይወትና ታሪክ ማጥናትና እነርሱን ለመምሰል መጣጣር መተኪያ የሌለው ጉዳይ እንደሆነ ተመልክተናል። እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በሚቀጥሉት ጊዜያት ከቅዱሳን ሐዋርያት ጀምሮ በየዘመናቱ የተነሡ ቅዱሳንን ታሪክ እናቀርባለን። ለዛሬ የቅዱሳን ሐዋርያትን ታሪክ መግቢያ እነሆ!
  ነቢያትን ትንቢት ያናገረ አምላክ፣ ወልደ አብ ወልደ ማርያም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም ሰው ሆኖ ከኃጢአት በስተቀር የሰውን ሥራ በመሥራት አደገ፡፡ በሠላሳ ዓመቱም በባርያው በዮሐንስ እጅ ተጠመቀ፡፡ በገዳመ ቆሮንቶስ መዓልትና ሌሊት ጾመ፤ ተራበ፤ ተጠማ፤ በዲያብሎስ ተፈተነ፡፡ ከዚህም በኋላ ወንጌለ መንግሥቱን ማስተማር ጀመረ፡፡ በሚያስተምርበት ወቅትም ለተለያዩ ዓላማዎች ብዙ ሕዝብ ( ገበያ ያህል) ይከተሉት ነበር። ግማሹይሤኒ ላህዩ እምውሉደ ዕጓለ እመሕያው- መልኩ ከሰው ልጆች ሁሉ ያምራልእንዲል /መዝ.452/ መልኩን ለማየት፤ ግማሹ በአምስት እንጀራና በሁለት ዓሣ አምስት ሺህ ሕዝብ ሲመግብ አይተው /ማቴ. 1416/ ሕብስት አበርክቶ ይመግበናል ብለው፤ ግማሹ ልዩ ልዩ ደዌ ያደረባቸውን ሰዎች በተአምራት ይፈውስ ነበርና ከበሽታቸው ለመፈወስ ይከተሉት ነበር /ማቴ.423/ ጌታችንም ከዚህ ሁሉ ሕዝብ መካከል መቶ ሃያ ቤተሰቦችን መረጠ። ምክንያቱ ደግሞ እነርሱ ከዋለበት እየዋሉ ካደረበት እያደሩ ትምህርቱን ሰምተው ተአምራቱን አይተው በሚገባ የሚከታተሉቀለምተማሪዎች ስለነበሩ ነው። ከእነዚህም ውስጥ አስቀድመው የተመረጡት ቅዱሳን ሐዋርያት ሲሆኑ (እርሱም ጸጋን ሰጠ፤ ከቤተሰቦቹም ሐዋርያትን፣ ከእነርሱም ነብያትንና የወንጌል ሰባኪዎችን ጠባቂዎችንና መምህራንን ሾመ። ኤፌ. ፬፣፲፬) በኋላ ፸፪ቱ አርድእት (ከዚህም በኋላ ሌሎች ሰባ ሰዎችን መረጠ ሉቃ. ፲፣፩) ቀጥሎ ደግሞ ፴፮ቱ ቅዱሳት አንስት ተመርጠዋል። ፲፪ + ፸፪ + ፴፮ = ፻፳ መቶ ሃያ ቤተሰብ የሚባሉ እነዚህ ናቸው።
  ሐዋርያ የሚለው ቃልሖረከሚለው የግዕዝ ግስ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙምለማስተማር የተላከማለት ነው፡፡ የአሥራ ሁለቱም ሐዋርያት ስም፡- ጴጥሮስ፣ እንድርያስ፣ ያዕቆብ፣ ዮሐንስ፣ ፊሊጶስ፣ በርተለሜዎስ፣ ቶማስ፣ ማቴዎስ፣ ያዕቆብ ወልድ እልፍዮስ፣ ታዴዎስ የተባለ ልብድዮስ፣ ስምዖን ቀኖናዊ እንዲሁም የአስቆሮቱ ይሁዳ ናቸው /ማቴ.101-4/፡፡    አባቶቻችን ቅዱሳን ሐዋርያት ምንም እንኳን ትውልዳቸው ከ፲፪ቱ ነገደ እስራኤል ቢሆንም የተመረጡት ግን በጌትነት ከሚኖሩ ከመሳፍንትና ከመኳንንት ወይም ከባለጸጎች ወገን ሳይሆን ከድሆች (ብዙዎች ሐዋርያት ዓሣ አጥማጆች ነበሩ) ካልተማሩትና በአጠቃላይ በኅብረተሰቡ ዘንድ ዝቅተኛ ስፍራ ከሚሰጣቸው ወገኖች ነበሩ። የዚህም ምክንያት ሐዋርያውወንድሞቻችን! እንግዲህ እንዴት እንደተጠራችሁ እዩ፤ በሥጋ እጅግ ብዙዎች ዐዋቂዎች አይደላችሁምና፤ ብዙዎች ኃያላንም አይደላችሁምና፤ በዘመድም ብዙዎች ደጋጎች አይደላችሁምና። ነገር ግን እግዚአብሔር ጥበበኞችን ሊያሳፍር የዚህን ዓለም ሰነፎች መረጠ፤ ኃይለኞችንም ያሳፍር ዘንድ እግዚአብሔር የዚህን ዓለም ደካሞች መረጠ። አለን የሚሉትንም ያሳፍር ዘንድ ዘመድ የሌላቸውን የተናቁትን፤ ከቁጥርም ያልገቡትን እግዚአብሔር መረጠብሎ እንደተናገረው ሰው በጥበቡና በኃይሉ በትውልዱም በእግዚአብሔር ፊት መመካት እንደማይገባው በተግባር ለማስገንዘብ ነው (፩ቆሮ. ፩፣፳፮- ፍጻሜ)
  ጌታችን እነዚህን መርጦ ሐዋርያት ብሎ ከሰየማቸው በኋላ (ከዕርገት በኋላ እርሱን ተክተው ሐዋርያት መደበኞች ሆነው አርድእት ደግሞ ሐዋርያትን እየረዱ የሚያስተምሩ ናቸውና!) ለጊዜው በምድረ እስራኤል ብቻ እንዲያስተምሩ ላካቸው፡፡ የዚህ ዓለም ወታደር ወደ ጦር ሜዳ ሲሄድ በቂ ስንቅና ትጥቅ እንደሚሰጠው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ለቅዱሳን ሐዋርያትበአሕዛብ መንገድ አትሂዱ ወደ ሳምራውያን ከተማም አትግቡ።  ነገር ግን ከእስራኤል ወገን ወደ ጠፉት በጎች ሂዱ። ሄዳችሁም መንግሥተ ሰማያት ቀርባለች እያላችሁ አስተምሩ። ድውያንን ፈውሱ፤ ሙታንንም አንሡ፤ ለምጻሞችንም አንጹ፤ አጋንንትንም አውጡ፤ ያለዋጋ የተቀበላችሁትን ያለዋጋ ስጡብሎ ድውይ የሚፈውሱበት፣ ሙት የሚያስነሡበት፣ ጋኔን የሚያወጡበት፣ ለምጽ የሚያነጹበት ሙሉ ትጥቅ ሰጣቸው፤መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችእያሉ እንዲያስተምሩም ላካቸው /ማቴ. ፲፣፭ - /  በተመሳሳይ ሁኔታ አርድእቱንም እንደላካቸው በሌላ ቦታ ተጽፎ እናገኛለን (ሉቃ. )
 ከዚህም በተጨማሪእነሆ እንደበጎች በተኩላዎች መካከል እልካችኋለሁ፤ እንግዲህ እንደእባብ ብልሆች እንድርግብም የዋሆች ሁኑ። ከክፉዎች ሰዎች ተጠበቁ፤ ወደ አደባባዮች አሳልፈው ይሰጧችኋልና፤ በምኩራቦቻቸውም ይገርፏችኋልናእያለ ወደፊት በስሙ ሲያስተምሩ ዓለም እንደሚጠላቸውና መከራ እንደሚያመጣባቸው፤ ይህንንም መከራ እንዴት እንደሚያሸንፉት ከነመፍትሔው ነገራቸው /ማቴ. ፲፣፲፯ ዮሐ. ፲፭፣፲፰- ፳፭/
  ከዚህ በኋላ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፅንስ የጀመረውን የማዳን ሥራ በሞቱ በቀራንዮ ፈጸመው፡፡ ዓለምን አድኖም መዓልትና ሌሊት በከርሠ መቃብር አድሮ ሙስና መቃብርን አጥፍቶ ተነሣ። ከትንሣኤው በኋላ ለሐዋርያት በጉባኤም በተናጠልም (ለአንዱ ለሁለቱ) እየተገለጸ ቀን አስተማራቸው። በ፵ኛው ቀን ኃይል፣ ጽንዕ የሚሆናቸው መንፈስ ቅዱስን እንደሚልክላቸው ተስፋ ሰጥቷቸው እስካሁን ያዩትንና የሰሙትን እውነት ለዓለም እንዲመሰክሩ አዝዟቸው ዐረገ። ባረገ በ፲ኛው ቀንም የተናገረውን የማያስቀር ጌታሁሉም መንፈስ ቅዱስን ተሞሉ፤ ይናገሩ ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እንዳደላቸው መጠንም እየራሳቸው በሀገሩ ሁሉ ቋንቋ ይናገሩ ጀመሩእንዲል ጰራቅሊጦስን (መንፈስ ቅዱስን) ሰደደላቸው /ሐዋ. / ጰራቅሊጦስ ማለት በፅርእ ቋንቋ የሚያጽናና የሚያስደስት ማለት ነው፡፡
 አባቶቻችን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ ፸፪ ቋንቋ ተገልጦላቸው በዕውቀት ጐለመሱ፤ ከብልየት ታደሱ፤ ፈሪዎች የነበሩ መከራ ሥጋን የማይፈሩ ጥቡዐን ሆኑ። መዲናቸው ኢየሩሳሌምን በኅብረት ካስተማሩ በኋላ ሑሩ ወመሀሩ- ሂዱና አስተምሩያላቸውን ቃል በመጠበቅ ዓለምን በዕጣ ተከፋፍለው አርድእት ደግሞ ሐዋርያትን ተከትለውአምላክ ከሰማያት ወረደ፤ በድንግልና ተፀንሶ በድንግልና ተወለደ፤ የምሥራችን አስተማረ፤ በአይሁድ እጅ ተገፈፈ ተገረፈ፤ በመስቀል ተሰቀለ፤ ሞተ፤ ተቀበረ፤ መቃብር ክፈቱልኝ መግነዝ ፍቱልኝ ሳይል በኃይሉና በሥልጣኑ በሦስተኛው ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሣ፤ በክብር በምስጋና ወደ ሰማይ ዐረገ፤ ዳግመኛም ለፍርድ ይመጣልብለው ወንጌልን ለዓለም ሁሉ ሰበኩ፤ ለቤተ ክርስቲያን ሕግ አወጡ፤ ሥርዓት ደነገጉ፡፡ ነቢዩ ዳዊትውስተ ኵሉ ምድር ወጽአ ነገሮሙ ወእስከ አጽናፈ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙትርጉሙምድምፃቸው ወደ ምድር ሁሉ ቃላቸውም እስከ ዓለም ዳርቻ ወጣብሎ የተናገረው ትንቢት ደረሰ፤ ተፈጸመ (መዝ. ፲፰ )
  ጌታችን በተራራው ስብከቱ ላይ ሲያስተምራቸውእናንተ የምድር ጨው፣ የዓለም ብርሃንና የተራራ ላይ መንደር ናችሁብሏቸው ነበርና በትምህርታቸው በትሩፋታቸው አልጫውን ዓለም በሃይማኖትና በአምልኮተ እግዚአብሔር አጣፈጡት። በኃጢአት ጨለማ ውስጥ የነበረውን የሰው ልጅ በንጽሕናና በቅድስና ወንጌል ብርሃን አበሩት። በድንቁርና ዋሻ ተሰውሮ የነበረውን የአሕዛብን ልብ በዕውቀት ተራራ ላይ አውጥተው ለዓለም ሁሉ እንዲገለጥና እንዲታይ አደረጉት። ይህን ሁሉ ሲያደርጉ የሐዋርያዊ አገልግሎታቸው ዋነኛ መሣሪያዎች ጌታቸውና መምህራቸው እንዳዘዛቸው ጥበብ፣ ትዕግሥት፣ ፍቅርና የዋህነት ነበሩ። በዚህ ሁኔታ የተመረጡለትን ታላቅ አምላካዊ ዓላማ አሳኩ፡፡ በኋላም የጌታቸውን አርአያ ተከትለው ያላመኑ አይሁድና አሕዛብ እኩሉን በገመድ እያነቁ፣ እኩሉንም በደንጊያ እየወገሩ፣ እኩሉንም በሰይፍ እየመቱ በልዩ ልዩ ዓይነት ስቃይ  እያሰቃዩ ገደልዋቸው፡፡ ሐዋርያትም ቁልቁል ተሰቅለው፣ በሰይፍ ተከልለው፣ እንደ በግ ተገፈው፣ በእሳት ተጠብሰው በድንጋይ ተወግረው ሰማዕትነትን ተቀብለው የመከራ ወንዝ የሆነ ይህን ዓለም ተሻገሩ፡፡ ሰውን ከሰው አላገናኝ ያለውን የቋንቋ፣ የጐሣ፣ የቅንዓትና የምቀኝነት ወንዝ ተሻግሮ እምነት፣ ተስፋ፣ ፍቅር ከሚገኝበት ከተማ የሚያደርሰውን ድልድይ ሠርተው ተልእኮአቸውን ጨረሱ፡፡የምሄድበት ጊዜዬ (ለሞት ዕድሜዬ) ደርሷል፡፡ መልካሙን ገድል ተጋድያለሁ፤ ሩጫውን ጨርሻለሁ፤ ሃይማኖትን ጠብቄአለሁ፤ ወደ ፊት የጽድቅ አክሊል ተዘጋጅቶልኛል፤ ይህንም ጻድቅ ፈራጅ የሆነው ጌታ ያን ቀን ለእኔ ያስረክባል፤ ደግሞም መገለጡን ለሚወዱት ሁሉ እንጂ ለእኔ ብቻ አይደለምበማለት መስክረው አለፉ /፪ጢሞ.፬፡፮-/፡፡
  ሐዋርያት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በአካል በዓይናቸው ያዩ፣ ቃሉን ከእግሩ ሥር ቁጭ ብለው የተማሩና በጆሮዎቻቸው የሰሙ፣ በእጃቸውም የዳሰሱት በአጠቃላይ ዓመት ከ፫ወር ሲያስተምር ከዋለበት እየዋሉ ካደረበት እያደሩ አብረውት የነበሩ፣ በኋላም ክርስቶስ በደሙ የመሠረታትን ቤተ ክርስቲያን አጥንታቸውን ከስክሰው፣ ደማቸውን አፍሰው፣ ሥጋቸውን ቆርሰው ስለገነቧት ቅድስት ቤተክርስቲያን ከፍተኛና ለየት ያለ ቦታ ትሰጣቸዋለች። ለመታሰቢያቸውም የቤተ ክርስቲያን ጣራ ፲፪ ዐምድ (ምሰሶ) እንዲኖረው ሊቃውንት ወስነዋል፡፡ ስለዚህ ሐዋርያት ከጌታችን ያዩትንና የሰሙትን ወንጌል ያስተላለፉ የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ስለሆኑ የቤተክርስቲያን መሠረቶች ናቸው። ከእነርሱ አስተምህሮና ትውፊት የወጣች ቤተክርስቲያን ቤተክርስቲያን ልትባል አትችልም። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስምእናንተ ግን የእኛን ፍለጋ ተከተሉ፤ እናንተስ እኛም ብንሆን ወይም መልአክ ከሰማይ ወርዶ እኛ ካስተማርናችሁ ወንጌል ሌላ ቢሰብክላችሁ ውጉዝ ይሁን። አስቀድሜ እንዳልሁ አሁንም ደግሜ እላለሁ ካስተማርናችሁ ሌላ ትምህርት ያስተማራችሁ ቢኖር ውጉዝ ይሁንበማለት ከሐዋርያት ትምህርት የሚወጣውን አስቀድሞ አውግዟል (ገላ. ፩፣ -)፡፡
   እግዚአብሔር ቢፈቅድና ብንኖር በቀጣይ ጊዜ የእያንዳንዱን ሐዋርያ ታሪክና ሐዋርያዊ ጉዞ በተከታታይ ለማቅረብ እንሞክራለን። ለዚህም የእግዚአብሔር ቸርነት፣ የእመ ብርሃን አማላጅነት፣ የቅዱሳን ሐዋርያት በረከታቸውና ረድኤታቸው አይለየን አሜን!!
         






Thursday, September 6, 2012

አሮጌውን ሰው አስወግዱ


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

የዚህ ትምህርት መሠረታዊ ዓላማ ክርስቲያኖች በአዲሱ ዓመት በክርስትና ሕይወታቸው እንዲያድጉ እንጂ በፊተኛ ኑሮአቸው እንዳይመላለሱ ከጨለማ ሥራ ጋርም እንዳይተባበሩ ለማሳሰብ ነው፡፡ ይህን ቃል የተናገረው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለኤፌሶን ክርስቲያኖች በጻፈላቸው መልእክቱ ነው /ኤፌ.4፡23/፡፡ 

  ኤፌሶን በሮም መንግሥት ሥር ሆና ታናሽ እስያ በምትባል አውራጃ በኤጅያን ባሕር ዳር /በዛሬዋ ኢያዘሎክ-ቱርክ/ የምትገኝ ታላቅ የንግድ፣ የአምልኮና የወደብ ከተማ ነበረች፡፡ በከተማዋ አርጤምስ /በላቲኑ አጠራር- ዲያና/ ለምትባል አምላክ ትልቅ መቅደስ ታንጾ ነበር /ሐዋ.19፡24፡27/፡፡ የባሕር አሸዋ የድሮይቱን ከተማ ስለሸፈናት ዛሬ ሰው አይኖርባትም፡፡ 

   ምንም እንኳን ክርስትና ወደዚህች ከተማ የገባው በጵርስቅላና በአቂላ አማካኝነት ቢሆንም /ሐዋ.18፡18-19/ ቤተ ክርስቲያኒቱ በይፋ የተቋቋመችው ግን ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በሦስተኛው ጉዞው ወደዚህች ከተማ መጥቶ ለሦስት ዓመት ያህል ወንጌል ካስተማረና ብዙ ሕዝብም ወደ ክርስትና ከመለሰ በኋላ ነው /ሐዋ.19፡8-27፣ 20፡31/፡፡ 

የኤፌሶን ከተማ ጢሞቴዎስ ጵጵስና የተሾመባትና በሰማዕትነት ያረፈባት፤ ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ሞትን ሳያይ የተሰወረባት፤ በኋላም በ431 ዓ.ም የንስጥሮስ ክሕደት በጉባኤ ተወግዞ የእመቤታችን ወላዲተ አምላክነት በይፋ የተመሰከረባት ከተማ ናት፡፡ 

ሐዋርያው መልእክቲቱን የጻፈላቸው ዋና ዓላማ አንደኛ የኤፌሶን ክርስቲያኖች ምንም እንኳን አሕዛብ ቢሆኑም ከእስራኤል ጋር አንድ ሆነው በክርስቶስ ጸጋ መዳናቸውንና ሰማያዊ ክብር ማግኘታቸውን አውቀው በእምነታቸው እንዲጠነክሩ ለማድረግ ሲሆን /ምዕ.1-3/ ሁለተኛው ደግሞ በክርስትና ሕይወታቸው እንዲያድጉ እንጂ በፊተኛ ኑሮአቸው እንዳይመላለሱ ከጨለማ ሥራ ጋርም እንዳይተባበሩ ለማሳሰብ ነው /ምዕ.4-5/፡፡ እኛም እግዚአብሔር እንደወደደና እንደፈቀደ በሁለተኛው ዓላማ ላይ በማተኰር እንማማራለን፡፡ ማስተዋሉን ያድለን!!

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በዚህ ምዕራፍና ቁጥር “ፊተኛ ኑሮአችሁን እያሰባችሁ እንደሚያታልል ምኞት የሚጠፋውን አሮጌውን ሰው አስወግዱ፤ በአእምሮአችሁም መንፈስ ታደሱ፤ ለእውነትም በሚሆኑ ጽድቅና ቅድስና እንደ እግዚአብሔር ምሳሌ የተፈጠረውን አዲሱን ሰው ልበሱ” ይላል /ኤፌ.4፡22-24/፡፡ 

   ምን ማለት ነው? አሮጌ ማለት ፊተኛ፣ የቀድሞ፣ የድሮ፣ የጥንት፣ ያረጀ ማለት ነው፡፡ ፊተኛ ኑሮ ማለትም የድሮ ባሕርይ፣ የቀድሞ ምልልስ ማለት ነው፡፡ የሰው ልጅ አሮጌነትን የተላበሰው በቀዳማዊ አዳም በደል ምክንያት ነው፡፡ ቀዳማዊ አዳም አስቀድሞ በእግዚአብሔር አርአያና አምሳል የተፈጠረ ንጽሐ ጠባይዕ ነበረው፡፡ መተዳደሪያውም ጽድቅ ብቻ ነበር፡፡ ሆኖም ግን ይህን እስከ መጨረሻ መጠበቅ አልቻለም፡፡ ሐዋርያው እንደነገረን  ዲያብሎስ ከቅንአት የተነሣ /ጥበብ.1፡24/ በእባብ አካል ተሰውሮ አዳምን በሚያታልል ምኞት ተፈታተነው /ዘፍ.3፡1/፡፡ ወደ እርሱ ፈቃድ ስቦም “አትብሉ” የተባሉትን የዛፍ ፍሬ ከሚስቱ ጋር እንዲበላ አደረገው፡፡ ያን ጊዜ አዳም ከክብሩ ተዋረደ፡፡ አሮጌ ሆነ፡፡ ባሕርዩ ወደ ኃጢአት ያዘነበለ ሆነና በእርሱ ጠባይ

Tuesday, September 4, 2012

እግዚአብሔር የተወሰኑ ሰዎችን ለመንግሥቱ ሌሎችን ደግሞ ለገሃነም ወስኗልን?


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

አንዳንድ ወገኖች የሰው ዕድል ፈንታው ጽዋዕ ተርታው ከጻድቃን ወይም ከኩንኖች መሆን አስቀድሞ በእግዚአብሔር የተወሰነ ነው በማለት ይናገራሉ፡፡ ለዚህ ቅድመ ውሳኔ /Predestination/ ሐሳባቸውም አስረጅ አድርገው የሚያቀርቧቸው መጽሐፍ ቅዱሳዊ ጥቅሶች አሏቸው /ሮሜ.911-21 ኤፌ.14/፡፡ ከዚህም በመነሣት ድኅነት የሚገኘው ከዘመናት በፊትእግዚአብሔር በወሰነው መሠረት እንጂ ሰው በሚፈጽመው ሥራ የማይሰጥ መሆኑን ይናገራሉ፡፡ እስኪ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን በዚህ ጉዳይ ምን ብላ እንደምታስተምርና የእነዚህ ሰዎች አስተምህሮ የሚያመጣው መጽሐፍ ቅዱሳዊ ተፋልሶ ምን እንደሆነ እንመልከት!

             1.አስቀድሞ ሁሉን ማወቅ ወይስ አስቀድሞ መወሰን?
 እግዚአብሔር ዓለምን ከመፍጠሩ በፊት እስከ ዓለም ፍጻሜ ሊሆን ያለውን ነገር ምንም ሳይሰወርበት ሁሉን ያውቃል፡፡ አንድ ሰው ከቅዱሳን ወገን አልያም ከኃጥአን ወገን እንደሚሆን አስቀድሞ ያውቃል /ሮሜ.828-30/፡፡ ሆኖም ግን የተወሰኑትን ለመንግሥተ ሰማያት የተወሰኑትን ደግሞ ለገሃነም ለኩነኔ አልፈጠራቸውም፡፡ እንዲህ ቢሆንስ ኖሮ እግዚአብሔር አንድስ እንኳ ይጠፋ ዘንድ እንደማይፈልግ ባለተናገረ ነበር /2ጴጥ.39/ የዓለም ሕዝብ በሙሉ ለድኅነት መጥራት ባላስፈለገ ነበር /ማቴ.2819 ሮሜ.819/ ሰዎች ሁሉ ይድኑ እውነትንም ያውቋት ዘንድ ባልወደደ ነበር /1ጢሞ.24/፡፡ በመሆኑም ሰው ከእግዚአብሔር በተቀበለው ነጻ ፈቃዱ ተጠቅሞ ወይ ርትዕት በሆነች የሕይወት መንገድ ይጓዛል አሊያም የሞት መንገድ በምትሆን በኃጢአት መንገድ ይሄዳል፡፡ ድኅነት ለሁሉም የተሰጠ ቢሆንም የሰው ድኅነቱ በራሱ መሻትና የነጻ ፈቃድ ምርጫ ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ ሄሬኔዎስ የተባለ አባትም፡- ጥቂቶች በተፈጥሮ ክፉ ቢሆኑ ሌሎችም መልካም ቢሆኑ መልካሞቹ ስለ መልካምነታቸው መልካም ሠሩ ተብለው ምስጋና የተገባቸው አይሆኑም፡፡ ሲፈጠሩ እንዲህ ሆነው ነውና፡፡ ክፉዎቹም ስለ ክፋታቸው ነቀፌታን ባላገኛቸው ነበር፡፡ ጥንቱንም ሲፈጠሩ እንዲህ ሆነዋልና ብሏል /Iraneus, Book IV, Chap.37/፡፡ 

             2. እግዚአብሔር አያዳላም ፍርዱም ርቱዕ ነው!
 እግዚአብሔር የተወሰኑ ሰዎችን ለመንግሥተ ሰማያት ሌሎችን ደግሞ ለገሃነም አስቀድሞ ወስኗል ማለት ክብር ምስጋና ለስም አጠራሩ ይሁንና እግዚአብሔር ያዳላል እንደማለት ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ግን አምላካችሁ እግዚአብሔር የአማልክት አምላክ፣ የጌቶች ጌታ፣ ታላቅ አምላክ፣ ኃያልም፣ የሚያስፈራም፣ በፍርዱም የማያዳላ፣ መማለጃም የማይቀበል ነው /ዘዳ.1017/ እግዚአብሔር ለሰው ፊት እንደማያዳላ በእውነት አየሁ /ሐዋ.1034/ ከእግዚአብሔር ዋጋችሁን እንደምትቀበሉ ታውቃላችሁ፤ ለክርስቶስ ትገዛላችሁና፤ የሚበድል ግን ፍዳውን ያገኛል እርሱም አያደላለትም ይላል /ቈላ.323/፡፡  

           3.አስቀድሞ መወሰን አለ ከተባለ ትእዛዛት ለምን ተሰጡ?
 እግዚአብሔር የተወሰኑትን ሰዎች ለመንግሥተ ሰማያት የተወሰኑትን ደግሞ ለገሃነም ፈጠረ ከተባለ ሰዎች በአእምሮ ጠባይ መሪነት፣ በሥነ ፍጥረት አስተማሪነት፣ በሕገ ልቡና አዋቂነት መልካም ሥራ መሥራት

Monday, September 3, 2012

እኔም አልፈርድብሽም- የዮሐንስ ወንጌል የ36ኛ ሳምንት ጥናት(8፡1-11)


 
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
  ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አይሁድ ከሚያከብሩት የዳስ በዓል በኋለኛው ቀን “ማንም የተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ፡፡ በእኔ የሚያምን መጽሐፍ እንዳለ የሕይወትን ውኃ ወንዝ ከሆዱ ይፈልቃል” ብሎ አሰምቶ ከነገራቸው በኋላ፣ አለቆቹና ካህናትም ክርክራቸውን ከፈጸሙ በኋላ /7፡53/ “ወደ ደብረ ዘይት ሄደ” /ቁ.1/። ካስተማርን፣ ከገሰጽን፣ ከመከርን በኋላ የራሳችን የሆነ የጽሞናና የጸሎት ጊዜ ሊኖረን እንደሚገባ ሲያስተምረን አንድም ማደርያው በዚያ ነበርና ወደ ደብረ ዘይት ሄደ /St. John Chrysostom/፡፡

  ከዚያ ሲጸልይ አድሮም እንደ ልማዱ ገስግሶ ወደ መቅደስ ሄደ /ቁ.2/፡፡  የመልካም አገልጋይ ባሕርይ እንዲህ ነው፡፡ መልካም አገልጋይ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል አገልግሎቱን በፍቅር ይፈጽማል፡፡ ስለዚህ ጌታ የሚወዳቸውን ልጆቹ ያገኝ ዘንድ ወደ ምኵራብ ገባ፡፡ “ሕዝቡም ሁሉ ወደ እርሱ ተሰበሰቡ”፡፡ ወንጌላዊው ሉቃስ “ሕዝቡም ሁሉ ይሰሙት ዘንድ ማልደው በመቅደስ ወደ እርሱ ይመጡ ነበር” እንዲል ትምህርቱን ያስተምራቸው ጀመር /ሉቃ.21፡38/፡፡

   በዚህ ጊዜ ጸሐፍትና ፈሪሳውያን ሕዝቡ የጌታን ትምህርት ያደምጡ ዘንድ እንዴት በጧቱ እንደተሰበሰቡ አዩ፡፡ ውስጣቸውም በቅንአት ተቃጠለና ትምህርቱን ያደናቅፉ ዘንድ ስትሴስን ያገኟትን አንዲት ሴት አስረው ይዘዋት መጡ፡፡ አምጥተውም ጌታ ካለበት ጉባኤ መካከል አቆሟት /ቁ.3/፡፡ ከዚያም “መምህር ሆይ!” ይሉታል /ቁ.4/፡፡ መምህርነቱን አምነውበት አልነበረም /7፡47/፡፡ አመጣጣቸው ለተንኰል ስለ ነበር እንጂ፡፡ ስለዚህ “ይህች ሴት ስታመነዝር ስትሴስን ተገኝታ ተያዘች (አግኝተን ያዝናት)፡፡ ሙሴም እንደዚህ ያሉት (አንድ ወንድ ለአንድ ሴት፤ አንዲት ሴት ለአንድ ወንድ ይሁን የሚለውን ሕግ ተላልፈው ቢገኙ) እንዲወገሩ አዘዘን፤ አንተስ ምን ትላለህ (ምን ትፈርዳለህ)?” አሉት /ቁ.5/፡፡  እንደነርሱ ሐሳብ ይህች ሴት ስትሴስን ስለ ተገኘች በዚህ ምድር በሕይወት መኖር “የማይገባት” ሴት ነች፡፡ የሚደንቀው ግን ይዘዋት የመጡት ወደ ይቅርታ አባቷ ወደ እግዚአብሔር መሆኑን አለማወቃቸው ነው፡፡ ይዘዋት የመጡት በዓለም ላይ እንዲፈርድ ሳይሆን ዓለምን እንዲያድን ወደ መጣው ጌታዋ

FeedBurner FeedCount