Wednesday, November 7, 2012

ተጐጂው ማን ነው?


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
                      (ጥቅምት 29/2005 ዓ.ም፣ በገ/እግዚአብሔር ኪደ)
  ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተራራው ስብከቱ ካስተማራቸው ትምህርቶች አንዱ “ጠላቶቻችሁን ውደዱ፤ የሚረግሙአችሁን መርቁ፤ ለሚጠሉአችሁም መልካም አድርጉ፤ ስለሚበድልዋችሁና ስለሚያሳድድዋችሁም ጸልዩ” የሚል ይገኝበታል /ማቴ.5፡43-44/፡፡
 ብዙዎቻችን ይህን ቃል ብናውቀውም ጠላቶቻችንን የምንወድበት፣ የምንመርቅበትና ስለ እነርሱ የምንጸልይበት ምክንያት ምን እንደሆነ ካለማስተዋላችን የተነሣ ይህን ለማድረግ እንቸገራለን፡፡ “ጌታ እንደዚያ እንድናደርግ ስላስተማረን ነው” በማለት እንደ ትእዛዝና ግዴታ ብቻ አድርገን የምንመለከተውም አንጠፋም፡፡
 ሆኖም ግን ከላይ የጠቀስነው የጌታችን ቃል እንዲህ የተባለበት የጠለቀ ምክንያት አለው፡፡ ይኸውም ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ጥያቄአዊ በሆነ አመክንዮ እንዲህ በማለት ያብራራልናል፡-

Tuesday, November 6, 2012

መቅረዝ -Mekrez: ስምህ

መቅረዝ -Mekrez: ስምህ:   “ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ! መንፈሳዊ ምስጋና ሁሉ ለአንተ ይገባል፡፡ ዋጋው የማይታወቅ ነጋዴ ገንዘቡን ሁሉ ሰጥቶ የተወዳጀው እውነተኛ ዕንቁ ደንጊያ አንተ ነህ፡፡ ይህንን ...

Sunday, November 4, 2012

ስለ አንድ የበግ ግልገል (ለሕፃናት)


           ወላጆች ይህን ትምህርት ለልጆችዎ ፕሪንት በማድረግ ወስደው ያንቡላቸው? 
 
ልጆች እንደምን ከረማችሁ? ትምህርትስ እንዴት ነው? ሰንበት ትምህርት ቤትስ ትሄዳላችሁ? ጎበዞች! ለዛሬ ደግሞ አንድ ቆንጆ ምክር ይዤላችሁ ስለመጣሁ በጽሞና ተከታተሉኝ፡፡ እሺ? ጎበዞች!
 ብዙ በጎች የነበሩት አንድ ሰው ነበረ፡፡ እህ… አላችሁ? ታድያ ይህ ሰው በጎቹን ሲጠብቅ በጣም ተጠንቅቆ ነው፡፡ የለመለመ ሳር ይመግባቸዋል፤ የጠራ ውኃ ያጠጣቸዋል፤ ወደ ተራራ ላይ ቢወጡ በጥንቃቄ ያወርዳቸዋል፤ የደከሙ ካሉ ደግሞ ይሸከማቸዋል፡፡ ወደ ማሳ ውስጥ እየገቡ ሳር ሲለቃቅሙ ደግሞ ባጠገባቸው ተቀምጦ ዋሽንት ይነፋላቸዋል፡፡ በጎቹም ዋሽንቱን እየሰሙ እጅግ ደስ ይላቸዋል፡፡

Saturday, November 3, 2012

የምንጽፍበት ሰሌዳ!


 በዲ/ን ዳንኤል ክብረት



በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
 ሁለት ጓደኞች ሞቃታማ በሆነው በረሃ እየሄዱ ነው። ብዙ ነገር እያነሡ ይወያያሉ። ታድያ የሆነ ጊዜ ወደ ክርክር ይገባሉ። አንዱ "እንዲህ ነው!" ሲል ሌላኛው "አይደለም" ይላል። "ነው" "አይደለም" "ነው" "አይደለም" እየተባባሉ ሲከራከሩ ፈርጠም ያለው ሌላኛውን በጥፊ አጮለው። በጥፊ የተመታው ደነገጠ። ቆይቶ ራሱን አረጋጋና ምንም ሳይናገር ቁጭ አለ። አጎንብሶም አሸዋው ላይ በጣቱ "ዛሬ በጣም የምወደው ጓደኛዬ በጥፊ መታኝ።" ብሎ ጻፈ። መቺው ቆሞ ያያል። ጓደኛውን በመምታቱና የተመታው ጓደኛውም ምንም ቃል አለመተንፈሱ ልቡን ነካው። ነገር ግን ይቅርታ እንኳ አላለውም።

FeedBurner FeedCount