Tuesday, September 10, 2013

የኢትዮጵያ የዘመን አቈጣጠር - ክፍል 2

ገ/እግዚአብሔር ኪደ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፥ መስከረም 1 ቀን፥ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

ዐውደ ዓመት
  ዐውደ ዓመት ማለት በፀሐይ 365¼ ዕለት፥ በጨረቃ 354 ዕለት ነው፡፡ ከፀሐይ ወሮች ዐጽፈ አውራኅ፥ ከጨረቃ ወሮች ደግሞ ሕጸጸ አውራኅ ይገኛል፡፡ ዐጽፈ (ድርብ፣ ዕጥፍ) አውራኅ ማለት በየወሩ 30 ቀን በሱባኤ ሲቀመር (ለሰባት ሲከፈል) የሚቀረው 2 ቀን በሌላው ወር ተደምሮ የሚቈጠር ስለሆነ ነው፡፡ ጨረቃ በዕለት፣ በ15 ቀን፣ በወርና በዓመት የምታጐድለው ቀንና ሰዓት ሕጸጽ ይባላል፡፡ ለምሳሌ በፀሐይ አቈጣጠር አንድ ወር 30 ቀን ሲሆን በጨረቃ ግን አንዳንዴ 29 ይሆናል፡፡ ይህ ጨረቃ ከፀሐይ የምታጐድለው አንድ ቀን ነው ሕጸጽ እያልነው ያለነው፡፡ ስለዚህ በፀሐይ አቈጣጠር ዐዲስ ዓመት መስከረም 1 ሲሆን በጨረቃ አቈጣጠር ግን ነሐሴ 24 ወይም ነሐሴ 25 ይሆናል ማለት ነው፡፡ [ጨረቃ ለ6 ወራት 29፣ 29 ትሆናለች፡፡ ስለዚህ 6 ቀን ታጐድላለች ማለት ነው፡፡ 5 የጳጉሜንን ዕለታትንም ጨምራ ስታጐድል በጠቅላላ 11፥ በየአራት ዓመት ደግሞ 12 ቀናት ታጐላለች፡፡ በዚህም ምክንያት በጨረቃ አቈጣጠር ዐዲስ ዓመት ነሐሴ 24 ወይም በየአራት ዓመት ነሐሴ 25 ይሆናል ማለት ነው፡፡]

የኢትዮጵያ የዘመን አቈጣጠር - ክፍል 1

ገ/እግዚአብሔር ኪደ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፥ ጳጉሜን 5 ቀን፥ 2005 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

መግቢያ

  የሰው ልጅ ሕይወት ከጊዜ ጋር በእጅጉ የተቈራኘ ነው፡፡ እያንዳንዱ ማኅበረሰብም የራሱ የሆነና ይህን ከሕይወቱ ጋር የተቈራኘውን ጊዜ የሚቀምርበት የዘመን አቈጣጠር አለው፡፡ ሊቃውንት ሲናገሩ “ለቃለ እግዚአብሔር ጥናት ሰዋስው፥ ለምስጋና ዜማ፥ ለምሥጢራት ቀኖና እንደሚያስፈልግ ሁሉ ለጌታ በዓላትም ባሕረ ሐሳብ የግድ ያስፈልጋል” ይላሉ፡፡ ኢትዮጵያም የራሷ የሆነ ሐሳበ ዘመን ማለትም የዘመን አቈጣጠር አላት፡፡ ይህ የዘመን አቈጣጠር (ሐሳበ ዘመን) የዘመናት፣ የዓመታት፣ የወራት፣ የሳምንታት፣ የዕለታት፣ የሰዓታት፣ የደቂቃዎች፣ የቅጽበትና (የካልዒትና) የመሳሰሉት ጊዜያት በሐሳብ የሚመዘኑበት፣ የሚሰፈሩበት፣ የሚቈጠሩበት ምድብና ቀመር ተሰጥቶአቸው የሚገኙበትን ውሳኔና ድንጋጌ እያሰማ የሚጠራበት ትምህርታዊ ውሳኔ ነው፡፡

Wednesday, September 4, 2013

« ርኢኩ ሰብዐተ መላእክተ እለ ይቀውሙ ቅድመ እግዚአብሔር » ራዕ 8÷2


                                                                             በክፍለ ሥላሴ 

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ጳጉሜ 1 ቀን፣ 2005 ዓ.ም.)፡-  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
መግቢያ
     ቅዱስ መጽሐፋችን «የእግዚአብሔር ቃል ሁሉ ተፈትናለች፣ እርሱ ለሚታመኑት ጋሻ ነው፡፡ እንዳይዘልፉህ ደግሞም ሐሰተኛም እንዳትሆን በቃሉ አንዳች አትጨምር» (ምሳ.30÷6) ይላል፡፡ ሰማያዊውን ወንጌል ቅዱሱን የእግዚአብሔር ቃል መንፈሳውያን በመንፈስ ቅዱስ ኃይል መሪነት መረመሩት፣ አመኑት አልፈውም ታመኑበት የጠላትን የክህደት ጦር ይመክቱበት ዘንድ ጋሻ ሆናቸው፡፡ ፈቃዳቸው እና የልባቸውም ሃሳብ የሚመራቸው ግን በገዛ መንገዳቸው ቃሉን ፈትነው የተከደነውን ሊገልጡ የተሰወረውን ሊያወጡ ቢባዝኑ ጥርጣሬን ጸንሰው ክህደትን ይወልዳሉ፣ ሀሰትን ጨምረው ተዘልፈው ይጠፋሉ፡፡ «ወንጌላችን የተከደነ ቢሆን እንኳ የተከደነባቸው ለሚጠፉት ነው»  (1ቆሮ 4÷3)፡፡

“ይህን ብታውቁ፥ ብታደርጉትም ብፁዓን ናችሁ” - የዮሐንስ ወንጌል የ48ኛ ሳምንት ጥናት (ዮሐ.13፡1-19)

ገ/እግዚአብሔር ኪደ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፥ ነሐሴ 29 ቀን፥ 2005 ዓ.ም.)፡- የነገረ መለኮት ሊቃውንት እንደሚያስተምሩት ከዚህ ከ13ኛው እስከ 17ኛው ምዕራፍ ያሉት የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፎች ጌታችን በምሴተ ሐሙስ ያደረጋቸውን የፍቅር ድርጊቶችንና ትምህርቶቹን አጠቃልለው ስለያዙ “የፍቅር ወንጌል” ብለው ይጠሩዋቸዋል፡፡ በእነዚህ ምዕራፎች ብቻ ወንጌላዊው “ፍቅር” እያለ 20 ጊዜ ጽፏል፡፡ የፍቅር ግብር ምሥጢረ ትሕትና የበለጠ የተገለጠው በዚህ ዕለት ነው፡፡ የፍቅር ማዕድ ምሥጢረ ቁርባን የተመሠረተው በዚህ ዕለት ነው፡፡ የምሥጢረ ጸሎት ትምህርትም በስፋት በጌቴ ሴማኒ የአታክልት ስፍራ የተማርነው በዚህ ዕለት ነው፡፡  እኛም ለዛሬ ከወንጌላዊው ጋር በሕፅበተ እግር ስለተገለጠው ስለ ምሥጢረ ትሕትና እንማማራለን፡፡ ምሥጢሩን ይግለጥልን!

FeedBurner FeedCount