Saturday, November 23, 2013

ጾመ ነቢያት

ገ/እግዚአብሔር ኪደ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፥ ኅዳር ፲፬ ቀን፥ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡-   በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
  “ጾም” በፊደላዊ ትርጕሙ- “ጾመ”፣ “ተወ”፣ “ታቀበ”፣ “ታረመ” ከሚለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ቃል ነው፡፡ የቃሉ ፍቺ ምግብ መተው፣ መከልከል፣ መታቀብ፣ መጠበቅ ማለት ነው፡፡ ቃሉ በዕብራይስጥና በሱርስት ቋንቋዎች “ጻም” ሲባል በዐረብኛ ደግሞ “ጻመ” ይባላል፡፡ ስለዚኽ ጾም ማለት ለክፉ ሥራ ከሚያነሣሱ የምግብ ዓይነቶች በቤተ ክርስቲያን የሥርዓት መጻሕፍት ከተወሰነው ጊዜ ሳያጓድሉ መከልከል ወይም ለተወሰነ ጊዜና ሰዓት ሰውነት ከሚያስፈልገው ነገሮች ሁሉ መወሰን (መታቀብ) ማለት ነው፡፡

Friday, October 18, 2013

አላዋቂ የያዘው መሣሪያ

በዲ/ን ብርሃኑ አድማስ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፥ ጥቅምት ፱ ቀን፥ ፳፻፮ ዓ.ም.፤ የጽሑፉ ምንጭ፡ አዲስ ጉዳይ መጽሔት፣ ቅጽ 7፣ ቁ.183፣ መስከረም 18 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡- የአምላክህ የእግዚአብሔር ቍጣ እንዳይነድድብህ ከምድርም ፊት እንዳያጠፋህ፥ በዙሪያችሁ ያሉት አሕዛብ የሚያመልኩአቸውን ሌሎችን አማልክት አትከተሉ” /ዘዳ.6፡15/ ተብሎ እንደተጻፈው እንኳን ሰው እግዚአብሔርም ይቆጣል፡፡ እግዚአብሔር የሚቆጣ መሆኑንና ተቆጥቶም የሚቀጣ መሆኑን ብዙ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ጥቅሶች አሉ፡፡ “ከቍጣው ጢስ ወጣ፥ ከፊቱም የሚበላ እሳት ነደደ፤ ፍምም ከእርሱ በራ” /መዝ.18፡8/፤የእግዚአብሔር ቍጣ በሕዝቡ ላይ ነድዶአል እጁንም በላያቸው ዘርግቶ መትቶአቸዋል፤” /ኢሳ.5፡25/ የሚሉትን የመሰሉ በመቶዎች የሚቈጠሩ ጥቅሶችን ከመጽሐፍ ቅዱስ እናገኛለን፡፡ እንዲሁም ከቅዱሳን ሰዎች ደግሞ ከታላቁ ነቢይ ከሙሴ ጀምሮ ያሉ ነቢያት ሐዋርያትና አበውም ሁሉ የሚቈጡባቸው አጋጣሚዎች ነበሩ፡፡ ለምሳሌ ቅዱስ ጳውሎስ ችሎት ፊት ቀርቦ እየተናገረ ባለበት ሰዓት ሊቀ ካህናቱ አፉን እንዲመቱት ሲያዝ፡- “አንተ በኖራ የተለሰነ ግድግዳ፥ እግዚአብሔር አንተን ይመታ ዘንድ አለው፤ አንተ በሕግ ልትፈርድብኝ ተቀምጠህ ሳለህ ያለ ሕግ እመታ ዘንድ ታዛለህን?”/ሐዋ.23፡3/ ሲል በቁጣ ቃል ተናግሮ ነበር፡፡ ስለዚህ ቁጣ በሁላችንም ሊገኝ የሚችልና በራሱም ከተፈጥሮአችን ጋር የሚቃረን ነገር አይደለም ማለት ነው፡፡

Wednesday, September 25, 2013

ነገረ መስቀል

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፥ መስከረም ፲፮ ቀን፥ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሓዱ አምላክ አሜን!!!
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ. ሥርዓት መሠረት ከመስከረም ፲ እስከ መስከረም ፳፭ ያለው ሳምንት “ዘመነ መስቀል” ይባላል፡፡ በዚህ ሳምንት ስለ መስቀል ክብር ይነገራል፤ መዝሙረ መስቀልም ይዘመራል፡፡ መስቀል ማለት “ሰቀለ” ከሚል የግእዝ ግሥ የተገኘ ሲኾን ትርጓሜውም “የተመሳቀለ፣ መስቀለኛ” ማለት ነው፡፡
 መቅድመ ወንጌል እንደሚነግረን፥ አዳም የማይበላውን በልቶ ከእግዚአብሔር አንድነት ከተለየ በኋላ አብዝቶ ያለቅስ ነበር፡፡ በኀጢአቱ ከማዘንና ከማልቀስ በቀርም ሌላ ግዳጅ አልነበረውም፡፡ በልብ መታሰቡ በቃል መነገሩ ከፍ ከፍ ይበልና ብዙ መጨነቁን፥ ጸዋትወ መከራዉን ያየው ቸሩ እግዚአብሔር ግን አዘነለት፡፡ “እቤዝወከ በመስቀልየ ወበሞትየ - በመስቀሌና በሞቴ አድንኀለኹ” ብሎም ቃል ኪዳን ገባለት /ኪዳነ አዳም ፫፡፫-፮፣ ዘፍ.፫፡፲፭/፡፡ መጽሐፈ ቀሌሜንጦስ እንደሚነግረንም ከ፭ ቀን ተኵል በኋላ እንደሚያድነው ተስፋ ሰጠው፤ ከ፭ ሺሕ ፭ መቶ ዓመታት በኋላ ሲል ነው፡፡ “ነገረ መስቀል” የምንለውም ይኸው ለአዳም የተሰጠው ተስፋ ነው፡፡

Friday, September 13, 2013

የኢትዮጵያ የዘመን አቈጣጠር - ክፍል 3 (የመጨረሻው ክፍል)



ገ/እግዚአብሔር ኪደ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፥ መስከረም 3 ቀን፥ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
 በዚህ ክፍል በአንዳንድ ምእመናን የሚጠየቁትን አንዳንድ ጥያቄዎች መልስ ለመስጠት እንሞክራለን፡፡
 ጥያቄ አንድ፡ - የኢትዮጵያ የዘመን አቈጣጠር ከአውሮፓውያን የዘመን አቈጣጠር ስለምን 7 ወይም 8 ዓመት ወደኋላ ይዘገያል?

FeedBurner FeedCount