Thursday, January 2, 2014

ነቢዩ ዘካርያስ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ታኅሳስ ፳፫ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡-በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
“ዘካርያስ” ማለት “ዝኩር፣ ዝክረ እግዚአብሔር - እግዚአብሔር ያስታውሳል” ማለት ነው፡፡ ይኸውም በምርኮ የነበሩትን አይሁድ እግዚአብሔር እንዳሰባቸው የሚያስገነዝብ ነው፡፡ በምስጢራዊ መልኩ ግን እግዚአብሔር ኹል ጊዜ በእኛ ውስጥ ያለችውን ቤተ መቅደስ (ነፍሳችንን) እንድናንፃት እንደሚያሳስበን፣ በመንፈሳዊ ተጋድሎአችን ኹሉ እንደሚረዳን የሚያስገነዝብ ነው፡፡

ነቢዩ ሐጌ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ታኅሳስ ፳፪ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡-በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
 ሐጌ ማለት በዓል፣ ደስታ ማለት ነው፡፡ የስሙ ትርጓሜ ሕዝቡ ከምርኮ የሚመለሱ ስለኾነ ይኽን ደስታ የሚያስረዳ ነው፡፡
 በብሉይ ኪዳን በመጨረሻ የምናገኛቸው ሦስቱን መጻሕፍት ማለትም ትንቢተ ሐጌ፣ ትንቢተ ዘካርያስና ትንቢተ ሚልክያስ ከምርኮ በኋላ ስላለው ጊዜ እንዲኹም አይሁድ ከምርኮ እንዴት ወደ አገራቸው እንደተመለሱ የሚያስረዱ ናቸው፡፡ በዚያ አንጻር ግን ደቂቀ አዳም ከዲያብሎስ ምርኮ እንደምን ወደ እግዚአብሔር እንደተመለሱ የሚያረዱ ናቸው፡፡

ነቢዩ ሶፎንያስ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ታኅሳስ ፳፩ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡-በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
 ሶፎንያስ ማለት “እግዚአብሔር ይሰውራል፣ እግዚአብሔር ይጠብቃል፣ እግዚአብሔር ይከልላል” ማለት ነው፡፡ “እናንተ ፍርዱን የጠበቃችሁ የምድር ትሑታን ኹሉ እግዚአብሔርን ፈልጉ፤ ትሕትናንም ፈልጉ፤ ምናልባት በእግዚአብሔር ቊጣ ቀን ትሰወሩ ይኾናል” እንዲል /፪፡፫/፡፡

ነቢዩ ዕንባቆም

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ታኅሳስ ፲፰ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡-በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ዕንባቆም ማለት ማቀፍ ማለት ነው፡፡ እግዚአብሔርን በጸሎት አቅፎታልና እንዲኽ ተብሏል፡፡ ሊቃውንት እንደሚመሰክሩት ነቢዩ ዕንባቆም ያላ ገባ ድንግል ሲኾን የቤተ መቅደስ ዘማሪ ነበር /ዕን.፫፡፩/፡፡

FeedBurner FeedCount