Wednesday, February 26, 2014

ዘወረደ ዘሐሙስ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 19 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ ጸልዩ እምቅድመ ንባበ ዝንቱ ክርታስ

ወገኖቼ ዛሬ በሐሙስ ዜማችን በእኔ ሳይሆን .ያሬድ ዛሬ ብዙውን ስለሚወራላት ቤተ ክርስቲያ በሰጣት የጅማሬ ሰላምታ በሀክሙ እላችኋለሁ። ሰላመ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር የሆነ ደስ ያላችሁ ሆይ ደስ ይበላችሁ እላለሁ።

ትናንት በረቡዕ ድርሰቱ ራስን መመርመር፣ ጾምን፣ መገዛትን፣ ምስጋናን፣ መውደድን ፣ የተራበን ማጥገብን፣ ለድሃውም መፍረድን መልካም እንደሆን ነግሮን እነዚህን ሁሉ ደግሞ በጾም ወቅት ማድረጉ የበለጠ ተገቢ ነውና ጾማችንን አብረን ቀድሰን እንድንፈጽም በሰላም መንገድ እንድንጓዝ ብሎን ለዛሬ አቀብሎን ነበረ።

ዘወረደ ዘረቡዕ




በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 18፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ ጸልዩ እምቅድመ ንባበ ዝንቱ ክርታስ

ሰላም ለሁላችሁ ይሁን ። በክርስቶስ ወገኖቼ የሆናችሁ ተወዳጆች በትናንት የማክሰኞ ድርሰቱ አባታችን ቅዱስ ያሬድ በፍቅርና በትህትና እንጹም ብሎ ጀምሮ በጾም ከአለም ልቀን ከፍ ከፍ እንድንል መክሮ ሳይተወን ከፍ ከፍ ማለታችን ደግሞ ምድራዊ ሕዋሳቶቻችንን ሁሉ በማጾም እንደሰማያዊ እንድንሆን ነው ካለን በኋላ በመጨረሻም በክርስቶስ መርቆን ተለያየን። ዛሬ በዕለተ ረቡዕ የሚያዜመውን ከዝማሜው ጋር እንደወትሮው ነፍሳችን ትሰማው ዘንድ እየጸለይን እንቀጥላለን።

ዘወረደ ዘሠሉስ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 17 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ
ጸልዩ እምቅድመ ንባበ ዝንቱ ክርታስ
 አባታችን በትናንት ሰኞ ዘወረደ ድርሰቱ አንዳየነው ከላይ በወረደው በጌታ ስም ጀምሮ በዓለም ታንቀንበት የነበረውን ያለፈውን የኃጢአት ገመድ አላቆ የጾምን ክብር በተለይም የዚህን ጾም ክብር ገልጦልናል።በመጨረሻም ተመለሱ ወደ እርሱም ቅረቡ እርሱም አለም ከሚሰጣችሁ ደስታ የተለየ ደስታ ይሰጣችኋል ብሎን ነበረ። ዛሬ ደግሞ በዛው ነፍሳችን በምትሰማው ሠማያዊ ዜማ የሚለን ነገር አለ።

ዘወረደ ዘሰኑይ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 16 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡-  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ ጸልዩ እምቅድመ ንባበ ዝንቱ ክርታስ

የብሉይ እና የሐዲስ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ከጸዋትወ ዜማ መጽሐፍቱ አንዱ በሆነው የድጓ ክፍል ጾመ ድጓ (በጾም ስለሚደረስ ጾመ ድጓ ተብሏል) ስለ ጾም ብዙ ጽፏል። ዛሬ ታዲያ እኔ የምፈቅደው እዚህ ያንን ሰማያዊ ዜማ ስለ ጾም በጾም ለጾመኞች እየተዜመ ብንሰማው ነበረ።ነገር ግን አሁን እሱን ማድረግ አንችልም። ነገር ግን ምንም እንኳን አባታችን በዜማ ያስተላለፈውን መልእክት በጽሁፍ መግለጤ ሰማያዊውን መልእክት ዋጋ እንዳያሳጣው ቢያስፈራኝም በጌታ ባለን ድፍረት እያነበብነው ለፍሳችን በነባቢት ባህሪይዋ ዜማውን እንድትሰማው እርሱ እንዲፈቅድ እየጸለይን ዛሬ ከሰኞ ዘወረደ ድርሰቱ በጥቂቱ የተመረጡ የጾም ቃላትን እያነበብን እንማማራለን። ግእዙን ብጽፈው የሀይለ ቃሉን ኀይል በተረዳነው ነበረ። ነገር ግን ይገባን ዘንድ በአማረኛ እስከገለጠልን ድረስ እናየዋለን

FeedBurner FeedCount