Tuesday, March 4, 2014

ቅድስት ዘረቡዕ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 25 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ
ጸልዩ እምቅድመ ንባበ ዝንቱ ክርታስ
 ‹‹ ሐዋዘ ብርሃነ እግዚኦ ነግሐ ነቂሐነ እምንዋም ንጊሣ ለቤተክርስቲያን ኃበ የኃድር ብዕለ ስብሐቲሑ ንስአል እም ሐቤሁ ረድኤተ ወሕይወተ ኩሉ ዘጌሰ ወመጽአ ኢይጻሙ - አቤቱ ያማረ ብርሐንን ስጠን፤ ነጋ ከእንቅልፋችንም ነቃን፤ የምስጋናው ሐብት ወደሚያድርባት ወደ ቤተ-ክርስቲያን እንገስግስ፤ የሁሉ ህይወት ከሚሆን ከእርሱም እርዳታን እንለምን፤ ወደ እርሷ የገሰገሰ የመጣም አይደክምም፡፡›› ቀኑን ሰላም አውሎ ሌሊቱን ሰላም አሳድሮ ትናንት የነበሩት በሌሉባት ዛሬ ነገን ተስፋ እናደርግ ዘንድ ጠብቆ ለዚህ ያደረሰንን አምላካችንን አመስግነን ቅዱስ ያሬድ እንደሚነግረን ስለማይነገር ስጦታው የምንከፍለው የሌለን በቤቱ በመገስገስ ህይወትን ለምነን አመስግነን በደስታ እንኖር ዘንድ አምላኬ እና መድኃኒቴ በሚሆን በክርስቶስ የመድኃኒቴ ዘውድ በሚሆን በአባቱ የቅድስናዬ መገኛ በሚሆን መንፈስ ቅዱስ በከበረች እናቴ የገነት ሙሽራ ድንግል ማርያም እንዲሁም ሰላማቸው በበዛ በማኅበረ ጻድቃን ስም ሁሉ ሰላማችሁ ይብዛ እላለሁ፡፡

Monday, March 3, 2014

ቅድስት ዘሠሉስ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 24 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ

ጸልዩ እምቅድመ ንባበ ዝንቱ ክርታስ

 ከልዑላን በላይ ልዑል፣ ከቅዱሳን በላይ ቅዱስ፣ የእርሱን ቅድስና ሌሎች ሲጠሩበት የእርሱ የማይከፈልበት፣ በአንድነት የሚመሰገን፣ በሦስትነት የሚቀደስ፤ ሠላምን በሞቱ፣ የገዛ ህይወትን በደሙ የመሰረተ፤ ቤቱን በማይፈርስ የሃይማኖት ምስክርነት ላይ ያነጸ፣ ቅዱሳን ተብለን ልንጠራ አባታችን ልንለው ሥልጣንን የሰጠን፣ ጸጋን ለሁሉ እንደችሎታ በሚያድለው አምላክ ስም ሁላችሁ በያላችሁበት ሰላሙ ይደረግላችሁ፡፡

Sunday, March 2, 2014

ቅድስት ዘሠኑይ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 23 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ
ጸልዩ ከምቅድመንባበ ዝንቱ ክርታስ

ይኄይሰኒ ሕገ አፉከ እምአእላፍ ወርቅ ወብሩር ወይጥእም እመዐር ወሶከር - ከብዙ ወርቅና ብር የአፍህ ህግ ይሻለኛል፡፡ እንደ ስኳርና እንደ ማር ይጥማልና፡፡በሚጥም አንደበቱ ጌታ አክብሮ አንደበቱን ያጣፈጠለት ዜመኛ የሰኞ ቅድስት ድርሰቱን ሲጀምር ባዜመበት ቃል ጀምረንንጉሰ ሰላም ሰላመከ ሀበነ - የሰላም ንጉሷ ሰላምህን ስጠንብለን እኛም ከእርሱ ጋር በማዜም በተሰጠን ሰላም ከዛሬ የድርሰቱን አንዳንድ ቃላትን እንላለን፡፡

Saturday, March 1, 2014

ቅድስት (ይህች ዕለት የተቀደሰች ናት)


(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 22 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ

ጸልዩ እምቅድመ ንባበ ዝንቱ ክርታስ
 ከአንድ ግንድ ላይ በቅለን ከአንዱ ከኢየሱስ ክርስቶስ አካል ሆነን ከአንዱ ከኢየሱስ ማዕድ የምንበላ የአንዱ አባት ልጆች የሆንን እንደ ብሉይ ሳይሆን በእርሱ ስም ተሰይመን በእርሱ ክርሰቲያን የምንባል አንድነታችን በሞት እንኳን የማይፈታ ቤተሰቦቼ ! ዘለዓለማዊ በሆነው በእርሱ ሰላምታ ደስታ ይሁንላችሁ እላላሁ ። ይህ የሚገባ ነውና ደስ ያላችሁ ደስ ይበላችሁ ብዬ ሰላምታዬን ወደ እናንተ ላክሁ።

FeedBurner FeedCount