Monday, March 24, 2014

ደብረዘይት ዘሠሉስ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 15 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 በደሙ ፈሳሽነት በተሰቀለው መስቀል ባርኮ ድኅነትን በሰጠን፣ የአባቴ ቡሩካን ሊለን በታመነ፣ ከሚመጣው የልቅሶ ሕይወት እንወጣ ዘንድ በፍቅሩ በጠራን፣ በክርስቶስ ስም ሰላም ለእናንተ ይሁን::

 ወአንሰ በብዝኀ ምሕረትከ ዕበውዕ ቤተከእኔ በምሕረትህ ብዛት ወደ ቤትህ እገባለሁ፤ አንተን በመፍራት በመቅደስህ ፊት እሰግዳለሁ፤ አቤቱ በጽድቅህ ምራኝ::” ፍጹም ወደ ሆነችው ቤተክርስቲያን በሌሊት አንቅተህ ጠራኸን:: ነገር ግን እንገባ ዘንድ የተገባን አይደለንም፤ የአንተ ቸርነት ለሁሉ የተገባን፣ የአንተ ጸጋ ለሁሉ የተጠራን ያደርገናል እንጂ::

ደብረዘይት ዘሠኑይ


በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 15 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 አስፈሪዋን ሰዓት እናልፍ ዘንድ ፍቀድልን:: በቀዳማይ ምፅአትህ በሥጋ ማርያም መገለጥህን አምነን በሕይወታችን አንተን መስለን በዳግማይ ምፅአትህም እንዳንተ የብርሃን ልብስን እንድንጎናጸፍ ፍቀድልን:: ያን ጊዜ ከሚያለቅሱትና ከሚተክዙት ሳይሆን የማይነገር ሰላምህን ከምትሠጣቸው አድርገን:: ዘላለማዊ ሰላሙን ይስጠን::

Friday, March 21, 2014

ደብረዘይት ዘሰንበተ ክርስቲያን



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 12 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 እኛ ክርስቲያን እንባል ዘንድ፣ ከክርስቲያኖችም ጋር እንኖር ዘንድ፣ በዘመናችንም ሁሉ እንደኖሩት ሐዋርያት ትምህርት እንኖር ዘንድ፣ እንደ አባቶቻችን ሐዋርያት ክርስቲያን ሆነን በመቃብር ውስጥ ባንቀላፋንም በዚያ በደብረዘይት በምንነሳም ጊዜ ከእነርሱ ጋር በእነርሱ እቅፍ እንቀመጥ ዘንድ በአንተ ፍቅር ልንኖር ግድ ይለናል:: በማይለወጥ ፍቅሩ ሰላም ለእናንተ ይሁን::

መጻጉዕ ዘቀዳሚት ሰንበት



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 12 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 በስሙ ስሙን አግኝታችሁ፣ በእርሱ የምትገቡ፣ ምርጦች ሆናችሁ የተጠራችሁ፣ የጨለማ ስራን አስወግዶ ወደሚደነቅ ብርሃን ያወጣችሁ፡፡ በይቅርታና በፍቅር ወደ እናንተ የመጣ ክርስቶስን ከላይ እንደ ልብስ ከውስጥ ደግሞ እንደ አካል የለበሳችሁት፣ ኃጢአትና ልምምዷን አሸንፎ በአባታዊ ፍቅር ልጅነትን ያደላችሁ ሁላችሁ በእርሱ በእግዚአብሔር ልጅ ሰላምታ ሰላም ይሁንላችሁ::

FeedBurner FeedCount