Saturday, April 5, 2014

ገብር ኄር ዘቀዳሚት ሰንበት

በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 27 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 በሦስትነት አንድ፣ በአንድነት ሦስት በሚሆን፣ በባሕርይ አንድ በሚሆን፣ በመለኮትም በሚተካከል በእግዚአብሔር ስም፣ በአንዲት ፈቃድ በሚተባበሩ በምሥጋና መብረቅ በተጋረዱ፣ በሚነድ እሳትም በሚሸፈኑ ጥንትና ፍጻሜ በሌለው በአንድ አምላክ ሰላም ይሁንላችሁ::

Thursday, April 3, 2014

ገብር ኄር ዘዓርብ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 25 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
 እንደ ሱራፌል ቃል በምናመሰግነው፣ የሰው ልጅ በማይነካው፣ የሟችም ሕሊና በማይመረምረው፣ በጽርሐ አርያም አትሮኑሱን ያኖረ፣ በተራሮች ራስ ላይ የጉምን ተን በሚያተን፣ ያለጩኸት በሚያስወግደው፣ በአየራት ውስጥ በሚያመላልሰው፣ ሰፊውን የሰማይ ገጽ የደመና ግምጃን በሚያላብሰው፣ ክብርና ምሥጋና በሚገባው በእግዚአብሔር ስም ሰላም ለእናንተ ይሁን::

ገብር ኄር ዘሐሙስ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 25 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 በማይለወጥ ሦስት፣ በማየረክስ ንጹሕ፣ በማያንቀላፋ ትጉህ፣ በማይደክም ብርቱ በሆነ በእግዚአብሔር ስም የመላክ ፍለጋ በሌለበት የነፋስን ፍጥነት በሚለካው በፍጥነቱም እንደጢስ ትንታ ጉምን በሚበትነው ለሥጋ ለባሽ ሁሉ ነፍስ ላላቸውም ሁሉ አምላክ በሆነ በአንድ እግዚአብሔር ስም ሰላም ለእናንተ ይሁን:: (መጽሐፈ ምሥጢር)

Tuesday, April 1, 2014

ገብር ኄር ዘረቡዕ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 23 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 የሕልውናው መሠረት በማይገኝ፣ በቁጥርም በማይቆጠር በእግዚአብሔር አብ ስም፣ የከዋክብት ብርሃን ሳይታይ የናጌብም ባሕር ጥልቅ ሳይሆን በፊት ከእርሱ ጋር በነበረና ያለ ሩካቤ ከድንግል ማኅጸን በተወለደ በአንድያ ልጁ ስም ሰላም ይሁንላችሁ::(መጽሐፈ ምሥጢር)

FeedBurner FeedCount