Tuesday, April 8, 2014

ኒቆዲሞስ ዘረቡዕ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 30 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
 የሕልውናው መጀመሪያ ከመቼ ጊዜ ጀምሮ ነው የማይባል፣ ስለመጨረሻውም እስከመቼ ሁሉን አሳልፎ ይኖራል የማይባል፣ ከኪሩቤልና ከሱራፌል አንደበት ለእርሱ ምሥጋና ይሁን:: ለእርሱም መስቀልን በማመን እየተመኩ ራሳቸውንም በወንጌል ቀንበር እያስገዙ በቤተመቅደስ እና በመገናኛው ድንኳን ከሚሰበሰቡ ከምዕመናን ሥግደት የሚገባው የሰላም አምላክ ሰላሙን ይስጣችሁ:: (መጽሐፈ ምሥጢር)

Monday, April 7, 2014

ኒቆዲሞስ ዘሠሉስ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 29 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 የኦሪት ሰንኮፍን ከእኛ ያራቅህልን፣ በሚደነቅ አጠራር ከጨለማ ጠርተህ የዳግም ልደትን የሠጠኸን፣ ሰውነታችን ሳይሆን ነፍሳችን የምትጠራበትን ሕጽበት ምሥጢር የገለጥክልን፣ በሌሊት ጨለማ ሕይወታችን ወደ አንተ እንገሰግሳለን፤ አንተም የጽድቅን የእውነትን ነገር ትገልጥልናለህ:: ከዚያም እውነትህን መመስከር እንጀምራለን:: በመጨረሻም ማንም በሌለበት ወቅት እንኳን ከመስቀልህ ስር ቅዱስ ሥጋህን እንገንዝ ዘንድ እንደ ኒቆዲሞስ ያለፍርሃት በጽድቅና በእውነት እንኖራለን:: ምክንያቱም በአንተ መኖር ያለውን ሰላም ከአይሁድ ተለይተን አይተናልና:: ይህ ሰላምህ ሁልጊዜ አብሮን ይኖር ዘንድ ፈቃድህ ይሁን::

ኒቆዲሞስ ዘሠኑይ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 29 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 ሰው በመሆናችን ልንሸከመው የማንችለውን ፍቅር ሰጠኸን፤ በጨለማ ሆነን አንተን ስንናፍቅ የማይጨልም ብርሃንን በሕይወታችን አበራህልን፤ የልባችንን ፍሬ መራራነት ታገስከን፤ የማስመሰላችንን ድራማ ቸል አልክልን፤ ስምህን ባጎደፍነው መጠን ሳይሆን በማይለካው ፍቅርህ ንጽሕናን አለበስከን፤ ፍቅርና ሰላም የለም ብለን ተስፋ በቆረጥን ጊዜ ይህ ነው በማይባል ሰዓት ደርሰህ እኛ የምንገረምበት እኛነት አደልከን፤ ሰላምን አጎናጸፍከን፤ በዚህ ሰላም ለሁላችሁ ሰላም ይሁን::

Saturday, April 5, 2014

ኒቆዲሞስ ዘሰንበተ ክርስቲያን



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 27 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 በሕልውና አንድ በሚሆን ሦስት፣ የማያገኙት ከፍ ያለ፣ የማያዩት የተሰወረ፣ የማይዙት እሳት፣ የማይዳስሱት መንፈስ፣ በማስተዋል የማይወስኑት ኃይል፣ የማይሾሙት ንጉሥ በሆነ በእግዚአብሔር ስም በመለኮቱ አምላካችን በቸርነቱም አባታችን ነው:: ለእርሱ ምሥጋና ይሁን:: በእርሱም የሆነ ሰላም ይብዛላችሁ::

FeedBurner FeedCount