Wednesday, May 28, 2014

ዕርገተ ክርስቶስ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ግንቦት ፳ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ከተነሣ በኋላ ዕለቱን ወደ ሰማይ አላረገም፡፡ ወንጌላዊው ሉቃስ እንደሚነግረን ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያረገው ከሙታን ተለይቶ ከተነሣ በኋላ በ፵ኛው ቀኑ ላይ ነው፡፡ በእነዚኽ ፵ ቀናት ውስጥም ብዙውን ጊዜ ለደቀ መዛሙርቱ እየተገለጠ ብዙ ምሥጢርና ሥርዓተ ሐዲስ አስተምሯቸዋል፡፡ የተማሩትን ኹሉ እንዲጠብቁ፣ ዓለምን ኹሉ በወንጌል መረብ እንዲያጠምዱ ትእዛዝ ሰጥቷቸዋል፡፡

Friday, May 16, 2014

ምክረ አበው ቁጥር 5



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ግንቦት ፰ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
1.  ጥያቄ፡- “ለሰው አፍ ከኮሶና ከነገር ማናቸው ይመራል?"
      ምላሽ፡- "ሲገባ ኮሶ ይመራል፤ ሲወጣ ግን ነገር ይመራል፡፡
2.  ሐሳብህ ብዙ የሚመኝ አንዱን ይዞ የማይሠራ ሲሆንብህ ሰይጣን በጐም ሥራ እንዳትሠራ ባለመሥራትህም እንዳትደነግጥ መልካምን በማሳሰብ እየከለከለ በጥበብ ሰንሰለቱ እንዳሰረህ ዕወቅ፡፡ ስለዚህ አንተ አንድ ሁነህ ሐሳብህን ብዙ አታድርግ፡፡ የምትኖርበትን የማትለቀው አንድ ሥራ ያዝ እንጂ ምኞትህን በየቀኑ አትለዋውጠው፡፡ አንዱን መያዝ አንዱን መልቀቅ የዕብደትና የዝሙት ነውና፡፡

Wednesday, May 14, 2014

መንፈሳዊ ሕይወት ከትንሣኤ እስከ ጰራቅሊጦስ - የመጨረሻው ክፍል



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ግንቦት ፮ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
5. እስክንገለጥ ድረስ ተሰውረናል

  ከማይበሉ የዓሣ ዝርያ ውስጥ የሚመደብ “ኦይስተር” የተባለ ዓሣ አለ፡፡ በሰውነቱ ውስጥም ለጌጣ ጌጥ የሚያገለግል ቅርፊት አለው፡፡ ነገር ግን ይኽ ዓሣ እስካልተገለጠ ድረስ ይኽ ክብሩ አይታይም፡፡ የእኛም እንደዚኹ ነው፡፡ ክርስቶስ እስካልተገለጠ ድረስ ክብራችን አይገለጥም፤ የተሰወረ ነው፡፡ ሕይወታችን ገና ያልተገለጠና የተሰወረ ከኾነ በዚኽ ዓለም መኖር ያለብን እንደሞተ ሰው ነው፡፡ ለምን? ሕይወታችን ክርስቶስ በክብር ሲገለጥ እኛም በክብር እንገለጥ ዘንድ፡፡

Monday, May 12, 2014

መንፈሳዊ ሕይወት ከትንሣኤ እስከ ጰራቅሊጦስ - ክፍል ፭



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ግንቦት ፬ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

4. እንገለጣለን፡፡
  እስከ ፍጻሜ ድረስ በዚኽ በተቀመጥንበት ስፍራችን የምንቈይ ከኾነ ክርስቶስ በክብር በሚገለጥበት ወራት በክብር እንገለጣለን፡፡ ከተቀመጥንበት ሰማያዊ ስፍራችን ለቅቀን የምንነሣ ከኾነ ግን የምንገለጠው ከክርስቶስ ጋር በክብር አይደለም፤ የዲብሎስን መልክ ይዘን በሐሳር ነው እንጂ፡፡ ስለዚኽ አኹን ከዚያ ስፍራ ለቅቆ መኖር የእኛ መገለጫ አይደለም፡፡ ይኽ ሕይወት ሌላ፣ ያም ሕይወት ሌላ ነውና፡፡ ክርስቶስ አኹን አልተገለጠም፡፡ የእኛም ሕይወት ገና አልተገለጠም፡፡ ስለዚኽ በክብር እስክንገለጥ ድረስ እዚያ ልንቈይ ያስፈልጋል፡፡ መቼ ነው ታድያ የምንገለጠው? ሕይወታችን ክርስቶስ በክብር ሲገለጥ፤ ዳግም ሲመጣ፡፡ እርሱ ሲገለጥ ሕይወታችን ይገለጣል፤ ክብራችን ይገለጣል፤ ደስታችን ይገለጣል፡፡

FeedBurner FeedCount