Friday, October 3, 2014

ትምህርተ ሃይማኖት (ክፍል ሦስት)

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መስከረም 23 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ከኹሉም በፊት አንድ ኦርቶዶክሳዊ ክርስቲያን ማወቅ ያለበት
 አንድ ኦርቶዶክሳዊ ክርስቲያን ከኹሉም በፊት ስለ ነገረ ቤተ ክርስቲያን፣ ስለ ቅዱስ ትውፊት፣ ስለ ቅዱሳት መጻሕፍት የአተረጓጐም ስልት፣ ስለ ዶግማ እና ስለ ቀኖና በጥቂቱም ቢኾን ማወቅ አለበት፡፡ አስቀድሞ ከእነዚኽ መሠረታውያን ትምህርቶች ጋር የተዋወቀ ክርስቲያን በትምህርተ ሃይማኖት (ዶግማ) ውስጥ ለሚኖረው ትምህርት መሠረትን ይይዛል፡፡ የእነዚኽን ጽንሰ ሐሳብ ያልተረዳ እንደኾነ ግን ጭራሽኑ የክርስትናን ጽንሰ ሐሳብም ሊስተው ይችላል፡፡ የብዙዎች ከቤተ ክርስቲያን መጥፋትም በአንድም ይኹን በሌላ መልኩ የእነዚኽ ኦርቶዶክሳዊ ጽንሰ ሐሳቦች የዕውቀት ማነስ ነው፡፡ ኹሉንም አንድ በአንድ የምንመለከታቸው ሲኾን ለዛሬ ከነገረ ቤተ ክርስቲያን እንዠምራለን፡፡

Thursday, October 2, 2014

ሰላም ተዋሕዶ

በብጹዕ አቡነ ጐርጐርዮስ ካልዕ የሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የነበሩ


ሰላም ተዋሕዶ ሰላም ኦርቶዶክስ
የአትናቴዎስ ሐውልት የዲዮስቆሮስ፡፡
  የአዳም መመኪያ የሔዋን ሀገር
  አንቺ አይደለሽም ወይ የቅዱሳን ክብር?
በከንቱ የሞተው የአቤል መሥዋዕት
የኄኖክ ሃይማኖት የአዳንሽው ከሞት
አንቺ የኖኅ መርከብ የሴም በረከት፡፡
  በአብርሃም ድንኳን ተወልደሽ ያደግሽ
  የይስሐቅ መዓዛ ወደር የሌለሽ
  ያዕቆብ በሕልሙ በቤቴል ያየሽ
  የዮሴፍ አጽናኙ ተዋሕዶ አንቺ ነሽ፡፡

Wednesday, October 1, 2014

ዓምደ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
ርዕይ፡-
ሕፃናትና ወጣቶች የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያንን ሕግና ሥርዓት ዐውቀውና አክብረው በሃይማኖትና በምግባር ጸንተው ሲኖሩ ማየት፤

ተልዕኮ፡-

ለሕፃናትና ለወጣቶች ወንጌልን በማዳረስ ለቤተክርስቲያን ተተኪዎችን ማፍራት፤

ዓላማ፡-

ወቅቱን ያገናዘቡ መንፈሳዊ የማስተማሪያ ዘዴዎችን በመጠቀም ሕፃናትና ወጣቶች የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያንን ትምህርተ ሃይማኖት ሥርዓተ እምነትና ክርስቲያናዊ ትውፊት እንዲያውቁና እንዲጠብቁ ማስተማር፤

Tuesday, September 30, 2014

ለይሖዋ ምስክሮች ኑፋቄ የተሰጠ ምላሽ (ክፍል አንድ)

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መስከረም 21 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
  የይሖዋ ምስክሮች የተባለው ተቋም እ.ኤ.አ. በ1870 ላይ የተመሠረተ ሲኾን፥ መሥራቹም ፔንሳልቫንያ በምትባለው የአሜሪካ ግዛት እ.ኤ.አ. በ1854 ላይ የተወለደው ቻርለስ ራስል የተባለ ግለሰብ ነው፡፡ ይኽ ሰው ከጓደኞቹ ጋር በየጊዜው እየተገናኘ መጽሐፍ ቅዱስ ያጠና ነበር፡፡ የኋላ ኋላ ግን በተለያዩ የክሕደት ትምህርቶች ውስጥ ወደቀ፡፡ ከክሕደቶቹ መካከልም “ነፍስ ትሞታለች፤ ሥላሴ የሚባል ትምህርት የለም፤ ወልድ ፍጡር በመለኮቱ፤ ክርስቶስ በሥጋ አልተነሣም፥ በፍጹም ሥጋም ወደ ሰማይ አላረገም፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ሚካኤል ነው፤ ዘለዓለማዊቷ ገነት ይኽቺ የምንኖርባት ምድር ነች፤ ኃጢአተኞች ፈጽመው ከመኖር ወዳለመኖር ይጠፋሉ እንጂ የዘለዓለም ስቃይ የሚባል አያገኛቸውም፥ ሰይጣንም ቢኾን ወደአለመኖር ይጠፋል እንጂ አይሰቃይም፤ መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ኃይል እንጂ አካላዊ አይደለም” የሚሉ ይገኙበታል፡፡ ለዚኹ ትምህርቱ ይረዳው ዘንድም መጽሐፍ ቅዱስን በማጣመም “የአዲሲቱ ዓለም መጽሐፍ ቅዱስ” በማለት የራሱ የኾነ መጽሐፍ አዘጋጅቷል፡፡ በአኹኑ ሰዓትም ይኽን የክሕደት ትምህርታቸውን በተለያዩ ቋንቋዎች በማዘጋጀት ብዙ ሰዎችን እያታለሉ ይገኛሉ፡፡ እኛም፥ እግዚአብሔር በፈቀደልን መጠን፥ እነዚኽ ተረፈ አርዮሳውያን በትምህርተ ሥላሴ ዠምረን ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች አንድ በአንድ መልስ እንሰጥበታለን፡፡ ለዚኽም እግዚአብሔር ዓይነ ልቡናችንን ያብራልን፤ አሜን!!!

FeedBurner FeedCount