Wednesday, December 31, 2014

“ነገር ኹሉ ለበጐ እንዲደረግ እናውቃለን” /ሮሜ.8፡28/

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐሙስ ታኅሳስ 23 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
  አንዳንዴ በሕይወታችን ምንም የማይጠቅሙ ነገሮችን ልንመርጥ እንችላለን፡፡ የሚያስፈልገንና የሚጠቅመን ግን መንፈስ ቅዱስ ሲመርጥልን ነው፡፡ አደጋና ስጋት፣ በሽታና ስቃይ፣ እጦትና ችግር፣ ራብና ጥማት፣ ኀዘንና ትካዜ የሌለው ሕይወት እጅግ ጠቃሚ እንደኾነ አድርገን እናስባለን፡፡ ነገር ግን ይኽ የሌለው ሕይወት ኹሉ ጠቃሚም ላይኾን ይችላል፡፡
  እስኪ የሐዋርያው የቅዱስ ጳውሎስን ሕይወት እንደ ምሳሌ አንሥተን እንመልከተው፡፡ እግዚአብሔር በሰጠው ሀብተ ፈውስ የዕውራንን ዐይን የሚያበራው፣ የለምጻሞችን ለምጽ የሚያነጻው፣ ሙታንን የሚያነሣው፣ ሌላ ይኽን የመሰለ ተአምራትን የሚያደርግ ታላቁ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ሥጋውን የሚጐስም የሰይጣን መልእክተኛ ነበረው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ የሰይጣን መልእክተኛ ያለው አባቶች በሦስት መንገድ ይተረጕሙታል፡፡ ሰይጣን ማለት ጠላት፣ ክፉ፣ ተቃዋሚ ማለት ነውና /1ኛ ነገ.5፡4/ ቅዱስ ጳውሎስ የሰይጣን መልእክተኛ ተሰጠኝ ሲል፡-

Tuesday, December 30, 2014

ለይሖዋ ምስክሮች ኑፋቄ የተሰጠ ምላሽ (ክፍል አራት)



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ማግሰኞ ታኅሳስ 21 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

የሥላሴ ትምህርት በጕባኤ ኒቅያ አበው
 ውድ የመቅረዝ ተከታታዮች እንደምን ሰነበታችኁ? በጥያቄና መልስ ዓምዳችን ለይሖዋ ምስክሮች የስሕተት ትምህርት ኦርቶዶክሳዊ ምላሽ መስጠት ከዠመርን የዛሬው አራተኛው ክፍል ነው፡፡ በክፍል አንድ ምላሻችን የይሖዋ ምስክሮች የስሕተት ትምህርቶች ምን ምን እንደኾኑ፥ እንዲኹም መሠረታዊ የምሥጢረ ሥላሴን ትምህርት በመጠኑ ዐይተናል፡፡ በክፍል ኹለት ክፍለ ጊዜአችንም ከብሉይ እና ከሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት በማመሳከር ምሥጢረ ሥላሴ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርት እንደኾነ ተመልክተናል፡፡ በክፍል ሦስትም ከሐዋርያነ አበው ዠምረን እስከ ሦስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበሩ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ምን ብለው እንዳስተማሩ ተመልክተናል፡፡ ስለ ቅድስት ሥላሴ የመጨረሻው ክፍል በኾነው በዛሬው ምላሻችን ደግሞ በአጠቃላይ በጕባኤ ኒቅያ የነበረውን ሒደትና ውሳኔ እንመለከታለን፡፡ ይኽን የምናደርግበት ምክንያትም በክፍል ሦስት ምላሻችን እንደነገርናችኁ የይሖዋ ምስክሮች የሥላሴ ትምህርት የተወሰነው በ325 ዓ.ም. በጉባኤ ኒቅያ በንጉሥ ቈስጠንጢኖስ አስገዳጅነት ነው ስለሚሉ ነው፡፡ እግዚአብሔር ዓይነ ልቡናችንን ያብራልን አሜን!!!

Saturday, December 27, 2014

ነገረ መላእክት (Angelology)



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ቅዳሜ ታኅሳስ 18 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ትርጕም
 ጥሬ ቃሉን ስንመለከተው መልአክ የሚለው የግእዝ ቃል ኹለት ትርጉሞች አሉት፡፡ አንደኛው አለቃ፣ ሹም ማለት ነው፡፡ በዮሐንስ ራዕይ ላይ የምናገኛው ሰባቱ የቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪዎች መላእክት ተብለው መጠራታቸውም ከዚኽ አንጻር ነው /ራዕ. 2 እና 3/፡፡ ኹለተኛውና ከተነሣንበት ርእስ አንጻር ስናየው ደግሞ መልክእተኛ፣ የተሰደደ፣ የተላከ የሚል ትርጕም አለው /ዕብ.1፡14/፡፡ ይኸውም የመላእክት ተግባር ምን እንደኾነ የሚያስረዳ ቃል ነው፡፡ መላእክት ከእግዚአብሔር ወደ ሰው፥ ከሰውም ወደ እግዚአብሔር የሚላላኩ መናፍስት ናቸውና፡፡ መላእክት በሌላ ስማቸው የሰማይ ሠራዊት ተብለው ይጠራሉ፡፡

Thursday, December 25, 2014

ወደ እግዚአብሔር ለመድረስ (ደረጃ ሦስት)



በዲ/ን ሳምሶን ወርቁ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐሙስ ታኅሳስ 16 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!


“እንደ እንግዳ መኖር”
 የተከበራችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች የመንግሥተ እግዚአብሔር ተጓዦች እንዴት ሰነበታችሁ? እነሆ ሦስተኛውን የመንፈሳዊ ሕይወት ደረጃ በምናባችን ዛሬ እንመለከታለን፡፡ አስቀድመን የመጀመሪያውን የመንፈሳዊ ሕይወት ደረጃ ጀርባችንን ለዓለም በመስጠት ጀምረናል፡፡ በመንገዱ ያሰበበት ለመድስ የሚጓዝ አሽከርካሪ በመንገድ እንዳይቀር በየደረሰበት ከተማ ነዳጅ እንደሚሞላ እኛም ተስፋ ወደምናደርጋት መንግሥተ እግዚአብሔር እስክንደርስ ድረስ በየደረጃዎቹ ላይ የምናገኛቸውን የቃለ እግዚአብሔር ስንቅ እየቋጠርን እንጓዛለን፡፡ በባለፈው ጽሑፍ “ከዓለማዊ መሻት መለየት” ሁለተኛውን የመንፈሳዊ ሕይወት ደረጃ ተመልክተናል፡፡ ከዓለማዊ መሻት መለየት በዓለም ካለው አላፊ ጠፊ ከሆነው ከገንዘብ ከሥልጣን ከዕውቀት ፍቅር ተለይተን፤ በምድር ላይ ስንኖር አለን የምንለው ነገር ሁሉ ከእኛ እንዳልሆነ አውቀን፤ ከራስ ወዳድነት ርቀንና ከውዳሴ ከንቱ ተለይተን መኖር ማለት መሆኑን ተመልክተናል፡፡

FeedBurner FeedCount