Friday, July 31, 2015

የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም ገዳም መምህራንና ቀሳውስት ማሠልጠኛ መንፈሳዊ ት/ቤት ትናንት፣ ዛሬና ነገ



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐምሌ 24 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኘው የታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም ገዳም መምህራንና ቀሳውስት ማሠልጠኛ ተቋም ከተመሠረተ ከ82 ዓመታት በላይ ኾኖታል፡፡ በእነዚህ አገልግሎት ዘመናቱም በርካታ ታላላቅ የሃይማኖት አባቶች ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቤተክርስቲያን ሊቃውንት፣ አባቶች መምህራንና ካህናትን አፍርቷል፡፡ ማሠልጠኛው ጥንታዊው የሀገራችን ቋንቋና ፊደል ግእዝና ትምህርቱ ተጠብቆ እንዲቆይ ለትውልድም እንዲተላለፍ በማድረግ በኩል ታላቅ ድርሻ አለው፡፡ የቤተክርስቲያን አባቶችና ምእመናን ኹሉ የቤተ ክርስቲያን አለኝታና ቅርስ መኾኑን በኩራት የሚናገሩለት ተቋም ነው፡፡
ይኼው ማሠልጠኛ በረጅም ጊዜ አገልግሎት ለቤተክርስቲያንም ኾነ ለሀገር ከፍተኛ አገልግሎትና ጥቅም የሰጠ ነው፡፡ በዚህም መሠረት የዚህን ት/ቤት ትናንት የነበረውን ገጽታ ዛሬ ያለበትንና ወደፊት የሚጠበቅበትን በዚህች አነስተኛ ጽሑፍ እንዳስሳለን፡፡

Sunday, July 26, 2015

....... ሰላም ገብርኤል.......



በልዑል ገ/እግዚአብሔር
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐምሌ 19 ቀን 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!


ሰላምታየሰላማዊ አካል ስጦታ
................
በጎነት አክብሮት ምሣሌው
የታላቅነት ትርጓሜ የሰሪውን ማንነት
...........
አንድ የመሆን ምስጢር ሲለው

ሰላም...!
ነገረ ፈጅ የእስራኤል ባለጠጋ
.........
መመረቅ መርገም ቢችልበት
ባላቅ ደስ ሊለው...
የፀጋውን ስጦታ ቅዱሱን ሊረግምበት
..............
አህያውን ይዞ ተጓዘበት

Tuesday, July 21, 2015

ትምህርተ ሃይማኖት (ክፍል ዐሥራ ሦስት)



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐምሌ 14 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
የእሑድ ሰዓተ መዓልት ፍጥረታት
ሀ) በአንደኛው ሰዓተ መዓልት፡- እግዚአብሔር በዚህ ጊዜ “ብርሃን ይኹን” ብሎ ብርሃንን በስተምሥራቅ በኩል ፈጠረ፡፡ ከዚህም በኋላ መንፈስ ቅዱስ ዓለምን እንደ እንቁላል በክንፉ ዕቅፍ አድርጐ ለመላእክት ታያቸው፡፡ መላእክቱንም እንዲህ ሲል ጠየቃቸው፡- “ይህ ኹሉ ሰማይ የእኔ ነው፡፡ ታዲያ ከቤቴ ማን አገባችሁ? ከወዴትስ መጣችሁ?” መላእከቱም፡- “አቤቱ ከግሩማን በላይ ያለህ ግሩም አንተ ነህ፡፡ በዚህን ያህል ድንጋፄ ያራድከን ያንቀጠቀጥከን እናውቅህ ዘንድ አንተ ማን ነህ?” አሉት፡፡ መንፈስ ቅዱስም “ሰማይን፣ ምድርን፣ እናንተንም ለፈጠረ ለአብ ሕይወቱ ነኝ” አላቸው /ኄኖክ.13፡21-22/፡፡ መላእክትም “አቤቱ ጌታችን የፈጠረንንስ፣ ያመጣንንስ ከቤትህስ ያገባንን አንተ ታውቃለህ እንጂ እኛ ምን እናውቃለን” ብለው ፈጣሪነቱ የባሕርዩ እንደኾነ አመኑለት፤ መሰከሩለት፡፡
ሳጥናኤልም መላእክትና መንፈስ ቅዱስ ሲነጋገሩ ቢሰማ ደነገጠ፤ ሐሳቡ ከንቱ ስለኾነበትም አፈረ /ኢሳ.14፡12-16/፡፡ ወዲያውም ያ በምሥራቅ የተፈጠረ ብርሃን እንደ ምንጭ እየፈሰሰ እንደ ጐርፍ እየጐረፈ ደርሶ አጥለቀለቃቸው፤ ዋጣቸው፡፡ ብርሃኑ የመጣው እግዚአብሔር ከአራቱ ባሕርያተ ሥጋ አንዲቱ ማለትም እሳቲቱን ብርሃን ውለጂ ብሎ ሲያዝዛት ነው፡፡ ከዚያም በኋላ ብርሃኑን መዓልት ብሎ ጠራው፡፡ ከዚያ በፊት ተፈጥሮ የነበረው ጨለማውን ደግሞ ሌሊት ብሎ ጠራው /ዘፍ.1፡5-6/፡፡ በዚሁም የብርሃንን ሥራና የጨለማ ሥራ ለይተን እንኖር ዘንድ ሲያስተምረን ነው፡፡

Monday, July 13, 2015

ትምህርተ ሃይማኖት (ክፍል ዐሥራ ኹለት)



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐምሌ 6 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ክሕደተ ሰይጣን
ሰይጣን በዕብራይስጥ ሲኾን ዲያብሎስ ደግሞ በግሪክኛ ነው፡፡ ትርጓሜውም አሰናካይ፣ ባለ ጋራ፣ ወደረኛ፣ ጠላት፣ ከሳሽ፣ ተቃዋሚ ማለት ነው፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በተቃወመው ጊዜ፡- “ወደኋላዬ ሒድ አንተ ሰይጣን፤ … ዕንቅፋት ኾነህብኛል” መባሉም ስለዚሁ ነው /ማቴ.16፡23/፡፡
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥም ከ40 በላይ በኾኑ የተለያዩ ስሞች ተገልጾ እናገኟለን፡፡ ጥቂቶቹን ለመጥቀስ ያህልም፡-
·         የቀድሞ ክብሩን ለመግለጽ - የአጥቢያ ኮከብ /ኢሳ.14፡12/፤
·         ምእመናንን እንዲሁ በሐሰት ይከሳልና- ከሳሽ /ራእ.12፡10/፤
·         ገዳይነቱንና ኃይለኝነቱን ለመግለጽ - ዘንዶ /ራእ.12፡3/፤
·         ክፋት እንዲበዛ የሚያደርግ ነውና - ክፉው /ማቴ.13፡19/፤
·         ከዋነኞቹ ግብሮቹ ለመግለጽ - ፈታኙ /ማቴ.4፡3/፤
·         የርኩሰት ጌታዋ ነውና - ብዔል ዘቡል /ማቴ.12፡24-27/፤
·         ወዘተርፈ
ሰይጣን እግዚአብሔርንና የእግዚአብሔር የኾኑትን ተቃውሞ የወደቀው የመጀመሪያው መልአክ ነው፡፡ ምንም እንኳን መልካም የኾነውን ኹሉ እየተቃወመ የራሱን መንግሥት ሊያቆም የሚጥር ቢኾንም ከእግዚአብሔር ጋር የተካከለ መንግሥት (መለኮታዊ ባሕርይ) የለውም፤ መለኮታዊ ባሕርይ የእግዚአብሔር ገንዘብ ብቻ ነውና፡፡

FeedBurner FeedCount