Thursday, July 21, 2016

ሰቆቃወ ቴዎፍሎስ በ‹‹ያ! ትውልድ›› መካከል … ‹‹ሞትህ ደጅ አደረ››! ክፍል አንድ…!

በአማን ነጸረ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐምሌ 14 ቀን 2008 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
የአቡነ ቴዎፍሎስ ዝክረ-ሥምዕ በቤተ ክህነቱም በአዲሱ ትውልድም ዘንድ እየተዘነጋ ሄደ፡፡እኛ ስንዘነጋው ታሪካቸው በቆናጽላን (ተሐድሶዎች) እንዳልሆነ-እንዳልሆነ ተተረከ፡፡የአቡነ ቴዎፍሎስን በመሥዋዕትነት የከበረ ታሪክ የቤ/ ታሪክ አድርጎ ለማየት ፍላጎት ጠፋ፤ሰቆቃቸው የሚዲያ ሽፋን ተነፈገ፡፡እንዲያ ተሰማኝ!ይሕን ሁሉ ችለን ሕመማችንን እንዳናስታምም ወዲህ ከቤተ ክህነት፣ወዲያ ከአብዮታውያን ወገን ያሉ ትሩፋን አበው ጭራሽ አጽመ-ቴዎፍሎስን በግፍ በወደቀበት እንበለ-ርኅራኄ አነወሩ፡፡ሲሻቸው ለቀ.. ተቆርቋሪ መስለው፣ሲሻቸው የሲሶ ግዛትን ተረክ ከለላ በማድረግ 2 ወገን በሚወረወር የብዕር ፍላጻ መቃብሩን እየፈለሱ በወደቀበት አለሳርፍ አሉት፡፡መንበሩን በግፍ ከለቀቀ 40 ዓመት የደፈነው ግፉዕ እረፍት አጣ፡፡ አላስተኛ አሉት፡፡ዘለግ ያለችውና መቼቷ 1953-1971 . የሆነው የዚህች ክታብምክንያተ-ጽሕፈትይኸው ነው--ሕማሙ፡፡የሚከተሉት አርእስት ለነዚህ ዐፅመ-ቴዎፍሎስን እንቅልፍ ለሚነሱ ልብ ሰባሪ ከሳሾች ‹‹እናንት የዛሬ ሕያዋን!ስለ ጉልበታችሁ አምላክ፤ሟች ሞቱን ይሙትበት፤ዐፅሙን ሰላም አትንሱ!›› ለማለት ያህል ከማስረጃ ጋር ተከረተሱ፡-
1.  የሲሶ ግዛት ተረክ …‹‹ሲሶ ግዛት›› ወይስ ‹‹የቶፋ ሥርዓት››?! 
2.  አብዮታዊ -አማኒነትና የአቡነ ቴዎፍሎስ ምዕዳን!
3.  ሰቆቃወ ቴዎፍሎስቅድመ-ሞት፣ጊዜ-ሞት፣ድኅረ-ሞት...ሞትህ ደጅ አደረ! 
4.  ዝክረ-ቴዎፍሎስ በአፈ-ጳጳሳት ወሊቃውንት!
የሚሉ አርእስትን መራኅያን አድርጌ በተቻለኝ መጠን ስሜቴን ገትቼ (እንዲያው መግታቱ ከሆነልኝ) የመዛግብቱን ሀቅ ለማሳየት እሞክራለሁ፤ለዚህም የአምላከ ግፉዐን ረድኤትና ጥበቃ እንደማይለየኝ አምናለሁ፡፡

Wednesday, July 20, 2016

አንተ ሰው እስኪ ንገረኝ!


በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐምሌ 13 ቀን 2008 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
አንድን የሥጋ ቁስል ለመፈወስ ለእያንዳንዱ ሰው ከባድ ነው፤ የነፍስን ቁስል መፈወስ ግን ለኹሉም ቀላል ነው፡፡ የሥጋ ቁስል ለመፈወስ መድኃኒት ብሎም ገንዘብ ያስፈልጋል፤ ነፍስን ለመፈወስ ግን ቀላል ብሎም ወጪን የማይጠይቅ ነው፡፡ ሥጋን ከዚያ ከሚያሰቃይ ቁስሉ ለመፈወስ አድካሚ ነው፡፡ ምክንያቱም በቀዶ ጥገና ምላጭ መቀደድ አለበት፤ መራራ መድኃኒቶችም ሊጨመሩበት ይገባል፡፡ ነፍስን ለመፈወስ ግን እንዲህ ዓይነት ነገር አያስፈልግም፡፡ ፈቃደኛ መኾን ብቻ በቂ ነው፤ ፍላጎቱ ካለ ኹሉንም ነገር ለማድረግ ቀላል ነው፡፡ የእግዚአብሔር መግቦቱም እስከ አሁን ድረስ ይህ ነው፡፡

Saturday, June 18, 2016

መቅረዝ ዘተዋሕዶ : በዓለ ጰራቅሊጦስ

መቅረዝ ዘተዋሕዶ : በዓለ ጰራቅሊጦስ: (መቅረዝ ዘተዋሕዶ፥ ግንቦት ፴ ቀን፥ ፳፻፮ ዓ.ም)፡ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!     “ጰራቅሊጦስ” ማለት በጽርዕ ልሳን “አጽናኝ” ማለት ነው፡፡ ምንም እንኳን በ፩ኛ ዮሐ.፪...

Wednesday, June 8, 2016

መቅረዝ ዘተዋሕዶ : ዕርገተ ክርስቶስ

መቅረዝ ዘተዋሕዶ : ዕርገተ ክርስቶስ: (መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ግንቦት ፳ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!! ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ከተነሣ በኋላ ዕለቱን ወደ ሰማይ አላ...

FeedBurner FeedCount