Sunday, December 25, 2011

ጸጋና እውነት በኢየሱስ ክርስቶስ ሆነ!!

(የዮሐንስ ወንጌል የአምስተኛው ሳምንት ጥናት)!!

“ዮሐንስ ስለ እርሱ መሰከረ እንዲህም ብሎ ጮኸ። ከእኔ በኋላ የሚመጣው እርሱ ከእኔ በፊት ነበረና ከእኔ ይልቅ የከበረ ሆኖአል፤ ስለ እርሱ ያልሁት ይህ ነበረ። እኛ ሁላችን ከሙላቱ ተቀብለን በጸጋ ላይ ጸጋ ተሰጥቶናልና ሕግ በሙሴ ተሰጥቶ ነበርና፤ ጸጋና እውነት ግን በኢየሱስ ክርስቶስ ሆነ። መቼም ቢሆን እግዚአብሔርን ያየው አንድ ስንኳ የለም፤ በአባቱ እቅፍ ያለ አንድ ልጁ እርሱ ተረከው።” ዮሐ.1፡15-18

የወንጌላዊውን ጥበብ ተመልከቱ! ምክንያቱም ስለ መጥምቁ ዮሐንስ ምስክርነት ደጋግሞ እየነገረን ያለው መጥምቁ በአይሁድ ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነት ስለነበረው ነው፡፡ ስለዚህ አይሁድ ክርስቶስን ላለመቀበላቸው ምክንያት ያጡ ዘንድ ስለሚወዱት ሰው ምስክርነት አብዝቶ ይነግራቸዋል /ማቴ.14፡4፣ ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ/፡፡ በእርግጥም መጥምቁ ዮሐንስ ከጌታ 6 ወር አስቀድሞ ነበር የመጣው /ሉቃ.3፡2-6/፡፡ ሲመጣም በቀስታ ሳይሆን እየጮኸ፣ በድብቅ ሳይሆን በግልጥ፣ ተገድዶ ሳይሆን ስለ ሰው ልጆች መዳን ብሎ ላንቃው እስኪሰነጠቅ ድረስ ይመሰክርላቸው ነበር /ኢሳ.40፡3/፡፡ ብዙዎችም ተከትለውታል፡፡ አማኑኤል ከመጣ በኋላ እንኳን ሕዝቡ የጌታን አምላክነት ባለመረዳታቸው “ዮሐንስ ይበልጣል” ብለው ስላሰቡ ከእርሱ አልለይ ያሉትን ደቀ መዛሙርቱ በጥበብ ወደ ሙሽራው ይልካቸው ነበር /ማቴ.16፡14፣ ማቴ.11 ሙሉ፣ ቅ.ቄርሎስ/፡፡ መጥምቁ በእነርሱ ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነት ቢያገኝም እርሱ ግን “የጫማውን ማዘብያ እንኳን መፍታት አይገባኝም” እያለ ራሱን ዝቅ ዝቅ በማድረግ ከእርሱ ወደሚልቀው ጌታ ሁሉም ዘወር ይሉ ዘንድ ይተጋ ነበር /ዮሐ.3፡22-30/፤ ራሱን ከፍ ከፍ ለማድረግ ዕድል የነበረው ቢሆንም ትሕትናው ግን ይህን ያደርግ ዘንድ አልፈቀደለትም /ዮሐ.1፡26፣ አውግስጢኖስ/፡፡

ወንጌላዊው ይቀጥልና “እኛ ሁላችን ከሙላቱ ተቀብለን በጸጋ ላይ ጸጋ ተሰጥቶናል” ይላል፡፡ እንዲህ ማለቱም ነበር፡- “ሦስት ዓመት ሙሉ ከክርስቶስ ጋር የተመላለስን ብቻ አይደለንም፡፡ አሥራ ሁለታችን፣ መቶ ሀያችን፣ ሦስት ሺው፣ ስምንት ሺው፣ አምስት ገበያው ሕዝብ ከክርስቶስ በረከት ተካፍለናል፤ የጸጋ ሥጦታው ከሆነው ከማዕዱ ተካፍለናል፤ ከሙላቱም ተቀብለናል፡፡ ስለዚህ ሁላችንም ምስክሮቹ ነን” /ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ/፡፡ በእርግጥም መጥምቁ ዮሐንስ ሲመሰክርለት የነበረው ጌታ ከጸጋ ተራቁተን ለነበርን ሁላችን ከመለኰታዊ ባሕርይው ሳይጐድል ጸጋውን ያድለን ዘንድ የመጣ ባለጸጋ ነው፤ ለዚህ የተገባን ሳንሆን ጸጋውን አደለን /ቅ.ቄርሎስ/፡፡ የሕይወታችን ምንጭ፣ የነፍሳችን ብርሃን ክርስቶስ! ጸጋውን ቢያድለንም ከራሱ ቀንሶ አይደለም፡፡ እርሱ የማይጐድልበት ባለጸጋ ነውና፤ የሚጐድለንስ ከእርሱ የተቀበልን እኛው ነን /ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ/፡፡
“በጸጋ ላይ ጸጋ ተቀበልን” ማለትስ ምን ማለት ነው? በእምነት ላይ የዘላለምን ሕይወት፣ በአእምሮ ጠባይዕ ላይ መንፈሳዊ አእምሮን፣ በአሥርቱ ቃላት ላይ ወንጌልን ተቀበልን ማለት ነው፡፡ አስቀድመን ክርስቶስን ስናምን ወደ ሕይወት ጐዳና እንገባለን፤ ቀጥለንም እምነታችንን ፍሬ እንዲያፈራ በፍቅር በሚሠራ እምነት ስናደርገው ቸርነቱ በዝቶልን የዘላለምን ሕይወት እንቀበላለን /ገላ.5፡6/፡፡ ስለዚህ በእርሱ ቸርነት በሚሠራ እምነት ላይ የዘላለምን ሕይወት ተቀበልን /አውግስጢኖስ/፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን እርሱ የእኛን ባሕርይ ስለተዋሐደ እኛም በመንፈሰ ረድኤት ላይ መንፈሰ ልደትን ተቀበልን /ቴዎዶር ዘሜውፕሳስትያ/፡፡

የሁለቱም ዮሐንስ ጥበብ ታስተውሉ ዘንድ እማልዳችኋለሁ!! ምክንያቱም መጥምቁ ዮሐንስ ራሱን ከጌታ ኢየሱስ ጋር ካነጻጸረልን በኋላ ወንጌላዊው ደግሞ ሙሴንና ክርስቶስን በንጽጽር በማስቀመጥ ይቀጥላል፡፡ በዚህ ጥበባቸውም ከእምነት ወደ እምነት እያሳደጉን ነው፡፡ መጥምቁ “እንደ ሰውነቱ ከእኔ በኋላ ይመጣል” ብሎ “እንደ አምላክነቱ ግን ከእኔ በፊት የነበረ ነው” ብሎ ከፍ ሲያደርገን፣ ወንጌላዊው ደግሞ “ሕግ በሙሴ ተሰጥቶን ነበረ” ይልና “ጸጋንና እውነትን ግን በክርስቶስ ተሰጠን” በማለት ያሳድገናል /ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ/፡፡ በእርግጥም ክርስቶስ ከሙሴ እንደሚበልጥ ሁሉ ወንጌልም ከኦሪት ትበልጣለች /ዕብ.3፡3/፡፡ ምንም እንኳን ኦሪት ራሷ ጸጋ ብትሆንም ክርስቶስ የሰጠንን ጽድቅና ፍጽምና ግን ልታመጣ አልቻለችም /ኢሳ.64፡6/፡፡ ከዚያ ይልቅ ኦሪት የምታስፈራራ ስትሆን ወንጌል ግን የምትፈውስ ናት /ገላ.3፡22፣ ዮሐ.12፡47/፡፡ ኦሪት ለፍርሐት የሚሆን የባርነትን መንፈስ ትሰጣለች፤ ወንጌል ግን አባ አባ የምንልበትን የልጅነትን መንፈስ ትሰጣለች /ሮሜ.8፡15/፡፡ ኦሪት በሥጋ የሚደረግ መገረዝን ታዝዛለች፤ ወንጌል ግን በመንፈስ የሚደረግ የልብ መገረዝን /ሮሜ.2፡29፣ 1ቆሮ.7፡19/፡፡ ኦሪት የረከሰውን በውኋ ብቻ ሰውነትን ታጠራለች፤ ወንጌል ግን በእሳትና በመንፈስ ቅዱስ አጥርታ ልጅነትን ትሰጣለች /ማቴ.3፡11/፡፡ ብዙ ማለት እንችል ነበር፤ ነገር ግን ጊዜ ሁናቴ ይገድበናል፡፡ በጥቅሉ ግን ሐዋርያው እንዲህ ይለናል፡- “ኃጢአትን ለምታስቆጥርና ለምታስኰንን ኦሪት ብዙ ክብር ከተደረገላት የጽድቅ መልእክት ለሆነችው ወንጌልማ ምን ያህል ትከብር ትመሰገን ይሆን?” /2ቆሮ.3፡9/፡፡ ይህም ማለት የሙሴ አገልግሎት “የኵነኔ አገልግሎት” ነበረች፤ በክርስቶስ የተቀበልነው ጸጋ ወንጌል ግን “የጽድቅ አገልግሎት” ነው /ቅ.ቄርሎስ/፡፡ በእርግጥም አሁን የተቀበልነው ጸጋ ኦሪት የያዘችውን ምሳሌና ጥላ ሳይሆን ወንጌል የያዘችውንና እውነት የሆነውን ክርስቶስን ነው /ጄሮም/፡፡

ወንጌላዊው፡- “መቼም ቢሆን እግዚአብሔርን ያየው አንድ ስንኳ የለም” ስላለ “የማይታይ ታየ” ብለን ከምናስተምረው ጋር የሚጋጭ አይደለም፡፡ እርግጥ ነው አንዳንድ ቅዱሳን አበው ወእማት በአንጽሖ መንፈስ አይተውታል፤ ሆኖም ግን በሚገባቸው ዓይነት፣ ምሳሌና ጐዳና እንጂ በመለኰታዊ ባሕርይው አይደለም /ዕብ.1፡1፣ አውሳብዮስ ዘቂሳርያ/፡፡ “መላእክቶቻቸው ሁል ጊዜ የአባቴን ፊት ያያሉ” የሚል ቃል እንኳን ብንሰማ መላእክት ሙሉዕ በኵለሄ የሆነውን እግዚአብሔር ለእነርሱ በሚመጥናቸው መጠን ይታያቸዋል ማለት እንጂ በውሱን ባሕርያቸው ጠንቅቀው ያዩታል ማለት አይደለም /ማቴ.18፡10/፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስም ይህንን የሚመስል ሐሳብ አስቀምጦልናል /1ጢሞ.3፡16፣ ቴዎዶሬት ዘስይርጥ/፡፡ ሕገ ኦሪትን የተቀበለ ሙሴ እንኳን ምንም እንደ ባልንጀራ ከእግዚአብሔር ጋር ቢነጋገርም ክብሩን እንጂ መለኰታዊ ባሕርዩን አላየም /ዘጸ.33፡11፣20/፡፡ አስቀድሞ ሕግን ለሙሴ የሰጠ ወልድ ግን አሁን ጸጋንና እውነትን ተመልቶ ወደ እኛ መጣ /አውግስጢኖስ/፡፡ መቼም ቢሆን ታይቶ የማያውቅ እግዚአብሔር አብም ልጁ ልጅ ሆኖ በባሕርዩ አይቶ ነገረን /ሄሬኔዎስ/፡፡ 

የተገለጠውና አባቱንም የገለጠልን ልጅ አንድ ነው፤ እኛ ግን ብዙዎች ነን፡፡ እርሱ የባሕርይ ልጅ ነው (By Nature)፤ እኛ ግን አባ አባ የምንልበት መንፈስ የተቀበልን የጸጋ ልጆች ነን (By Adoption) /ሮሜ.8፡15/፡፡ አዎ! አካላዊ ቃል አባቱ ስለ ሁላችን ቤዛ አድርጐ የሰጠን አንድ ልጅ ነው /ሮሜ.8፡32፤ አውግስጢኖስ/፡፡ ስለዚህ አብን ያየው ይህ በአብ ዕሪና ያለው አንዱ ልጁ ብቻ ነው /ዮሐ.6፡46፣ ቅ.ቄርሎስ/፡፡ ከእርሱ ውጪ የአባቱን እቅፍ ጠንቅቆ የሚያውቅ የለም /ማቴ.11፡27፣ አውግስጢኖስ/፡፡ የአባቱ እቅፍ ስንልም መለኰታዊ ባሕርይውን ማለታችን ነው፡፡ ይህ ማለት ግን እግዚአብሔር ራሱን ለዓለም የገለጠው በልጁ በኩል ብቻ ነው ማለት ሳይሆን ከሌሎች መገለጦች ይልቅ በልጁ በኩል የተገለጠው መገለጥ ፍጹም ነው፤ እንደሌሎቹ መገለጦች ሕጸጽ የለበትም ማለታችን እንጂ /ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ/፡፡ 

ተወዳጆች ሆይ! የተደረገልንን ውለታ ተመልከቱ፡፡ እግዚአብሔር እንደ ድሮው በነብያት አልተናገረንም፤ በአንድ ልጁ በኵል እንጂ /ዕብ.1፡1/፡፡ የእነዚያ መምህር ሙሴ ነበር፤ የእኛ መምህር ግን የሙሴ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ እንግዲያስ ለዚሁ ጌታ የተገባን ሆነን ልንገኝ ያስፈልጋል፤ በዚሁ ምድር መንፏቀቅ ሊበቃን ይገባል፡፡ እርሱ ከልዕልናው ዝቅ ብሎ ያናገረን እኛ ከምድራዊ አስተሳሰብ እንላቀቅ ዘንድ ነውና፤ እርሱ በሄደበት ጐዳና እንድንመላለስ ነውና፡፡ “ይህንን እንዴት ማድረግ እችላለሁ?” ብላችሁ አትጨነቁ፡፡ ከእኛ የሚፈለገው ፍቃድ ብቻ ነው፤ ሠሪው ግን እግዚአብሔር ራሱ ነው /ዮሐ.15፡5/፡፡ ስለዚህ እርሱ እንደ ወደደን እርስ በእርሳችን እንዋደድ፡፡ “እኔ እንዲህ ዓይነት ሰው አልወድም፤ እንዲህ ዓይነቱ ሰው ያሥጠላኛል፤ እኔ እርሱን ልወደው አልችልም” እያልን ራሳችንን አናታልል፡፡ ምክንያቱም እንዲህ የምንለው ሰውዬ እንደ እኛ በአርአያ ሥላሴ የተፈጠረ፣ ክርስቶስም ዋጋ የከፈለለት ክቡር ሰው ነውና፡፡ ክርስቶስ ለሁለታችን መዳን መጣ እንጂ ለእኛ ብቻ አይደለም፡፡ ስለዚህ እንደ እግር፣ እጅ፣ አፍንጫ… በአንድ ክርስቶስ ያለን ብልቶች እንጂ የተለያየን አይደለንም፡፡ ሐዋርያው “እኛ ሁላችን በአንድ መንፈስ አንድ አካል እንድንሆን ተጠምቀናል” እንዲል /1ቆሮ.12፡13/፡፡ እንግዲያስ “ማንም የገዛ ሥጋውን የሚጠላ ከቶ የለምና” /ኤፌ.5፡29/ በአንዲት ተዋሕዶ ሥር ሆነን ሳለ አንቦጫጨቅ፤ አንነካከስ፤ አንድ እንሁን፤ እንደ ቅርጫ ሊከፋፈሉን የሚያሰፈስፉ ክፉ መናፍስትን ከእኛ እናርቅ፡፡ እኛ ስንዋደድ የሰማዩ አባታችን እግዚአብሔር ይከብራል፤ እንዲህ ካልሆነ ግን በአሕዛብ ዘንድ ስሙን እናሰድባለን፡፡ መልካሙን ሁሉ እንድናደርግ ሰውን በመውደድ ሰው የሆነው ክርስቶስ ይርዳን፡፡ አሜን!!
 
ሰላም ወሰናይ (በስድስተኛው ሳምንት ሰላም ያገናኘን)!

የዮሐንስ ወንጌል የ2ኛ ሳምንት ጥናት
የዮሐንስ ወንጌል የ3ኛ ሳምንት ጥናት
የዮሐንስ ወንጌል የ6ኛ ሳምንት

Glory to God for All Things ( St. John Chrysostom)

« Angels Sing Bowing in Bethlehem »


BEHOLD a new and wondrous mystery. My ears resound to the Shepherd’s song, piping no soft melody, but chanting full forth a heavenly hymn. The Angels sing. The Archangels blend their voice in harmony. The Cherubim hymn their joyful praise. The Seraphim exalt His glory. All join to praise this holy feast, beholding the Godhead here on earth, and man in heaven. He Who is above, now for our redemption dwells here below; and he that was lowly is by divine mercy raised.


Bethlehem this day resembles heaven; hearing from the stars the singing of angelic voices; and in place of the sun, enfolds within itself on every side, the Sun of justice. And ask not how: for where God wills, the order of nature yields. For He willed; He had the power; He descended; He redeemed; all things yielded in obedience to God. This day He Who is, is Born; and He Who is, becomes what He was not. For when He was God, He became man; yet not departing from the Godhead that is His. Nor yet by any loss of divinity became He man, nor through increase became He God from man; but being the Word He became flesh, His nature, because of impassability, remaining unchanged.


And so the kings have come, and they have seen the heavenly King that has come upon the earth, not bringing with Him Angels, nor Archangels, nor Thrones, nor Dominations, nor Powers, nor Principalities, but, treading a new and solitary path, He has come forth from a spotless womb.


Since this heavenly birth cannot be described, neither does His coming amongst us in these days permit of too curious scrutiny. Though I know that a Virgin this day gave birth, and I believe that God was begotten before all time, yet the manner of this generation I have learned to venerate in silence and I accept that this is not to be probed too curiously with wordy speech. 

For with God we look not for the order of nature, but rest our faith in the power of Him who works.
What shall I say to you; what shall I tell you? I behold a Mother who has brought forth; I see a Child come to this light by birth. The manner of His conception I cannot comprehend. 

Nature here rested, while the Will of God labored. O ineffable grace! The Only Begotten, Who is before all ages, Who cannot be touched or be perceived, Who is simple, without body, has now put on my body, that is visible and liable to corruption. For what reason? That coming amongst us he may teach us, and teaching, lead us by the hand to the things that men cannot see. For since men believe that the eyes are more trustworthy than the ears, they doubt of that which they do not see, and so He has deigned to show Himself in bodily presence, that He may remove all doubt.

Christ, finding the holy body and soul of the Virgin, builds for Himself a living temple, and as He had willed, formed there a man from the Virgin; and, putting Him on, this day came forth; unashamed of the lowliness of our nature. 

For it was to Him no lowering to put on what He Himself had made. Let that handiwork be forever glorified, which became the cloak of its own Creator. For as in the first creation of flesh, man could not be made before the clay had come into His hand, so neither could this corruptible body be glorified, until it had first become the garment of its Maker. 

What shall I say! And how shall I describe this Birth to you? For this wonder fills me with astonishment. The Ancient of days has become an infant. He Who sits upon the sublime and heavenly Throne, now lies in a manger. And He Who cannot be touched, Who is simple, without complexity, and incorporeal, now lies subject to the hands of men. He Who has broken the bonds of sinners, is now bound by an infants bands. But He has decreed that ignominy shall become honor, infamy be clothed with glory, and total humiliation the measure of His Goodness. 

For this He assumed my body, that I may become capable of His Word; taking my flesh, He gives me His spirit; and so He bestowing and I receiving, He prepares for me the treasure of Life. He takes my flesh, to sanctify me; He gives me His Spirit, that He may save me. 

Come, then, let us observe the Feast. Truly wondrous is the whole chronicle of the Nativity. For this day the ancient slavery is ended, the devil confounded, the demons take to flight, the power of death is broken, paradise is unlocked, the curse is taken away, sin is removed from us, error driven out, truth has been brought back, the speech of kindliness diffused, and spreads on every side, a heavenly way of life has been ¡in planted on the earth, angels communicate with men without fear, and men now hold speech with angels. 

Why is this? Because God is now on earth, and man in heaven; on every side all things commingle. He became Flesh. He did not become God. He was God. Wherefore He became flesh, so that He Whom heaven did not contain, a manger would this day receive. He was placed in a manger, so that He, by whom all things arc nourished, may receive an infant¢s food from His Virgin Mother. So, the Father of all ages, as an infant at the breast, nestles in the virginal arms, that the Magi may more easily see Him. Since this day the Magi too have come, and made a beginning of withstanding tyranny; and the heavens give glory, as the Lord is revealed by a star.

To Him, then, Who out of confusion has wrought a clear path, to Christ, to the Father, and to the Holy Ghost, we offer all praise, now and for ever. Amen.

Saturday, December 24, 2011

የቃል ሰው የመሆን ምሥጢር (የዮሐንስ ወንጌል የአራተኛው ሳምንት ጥናት)!!

(አዘጋጅ፡- ገብረ እግዚአብሔር ኪደ)!

“ቃልም ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ አደረ፥ አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነው ክብሩን አየን።” ዮሐ.1፡14

የሰው ልጆች የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ የእግዚአብሔር ልጅ የሰው ልጅ ሆነ፤ ከጸጋ ርቀን በጨለማ ለነበርን ሁላችንም ወደማይነገር ክብር ከፍ ከፍ አደረገን /መዝ.88፡27/፡፡ አንድ ባለ ጸጋ ንጉሥ ከዙፋኑ ወርዶ ድሆችን እንደሚጐበኝና ምንም ሳይጸየፍና ሳያፍር አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርግላቸው አካለዊ ቃል እግዚአብሔር ወልድም በኃጢአት ምክንያት ከጸጋ ተራቁተን ለነበርን ሁላችን ሳይንቀንና ሳይጸየፈን በምሕረቱ ጐበኘን፤ ባለ ጸጋ ሲሆን ስለ እኛ ድሀ ሆነ /2ቆሮ.8፡9፣ ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ/፡፡ ነገር ግን የጨው ሐውልት እንደ ሆነች እንደ ሎጥ ሚስት አይደለም /ዘፍ.19፡26/፤ የበረሀ አውሬ እንደሆነ ዳግመኛም ሰው ወደ መሆን እንደተለወጠው እንደ ከላውዴዎስ ንጉሥ እንደ ናቡከደነጾር አይደለም /ዳን.4፡28-34/፤ ወይን እንደሆነ እንደ ቃናም ውኃ አይደለም /ዮሐ.2፡6-9፣ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ/፡፡ የእግዚአብሔር ቃልና የሥጋ ባሕርይ በተዋሕዶ አንድ ሆነ እንጂ /ቅ.ጐርጐርዮስ ዘእንዚናዙ/፡፡

ዘመን የማይቈጠርለት የእግዚአብሔር ልጅ የሰው ልጅ እንደሆነ እናውቃለን፤ ነገር ግን እንዴት ወንድ ከማታውቅ ድንግል እንደተወለደ፤ ረቂቅ ሲሆን እንዴት እንደገዘፈ፤ በረድኤት ሳይሆን እንዴት የኵነት ሥጋ እንደሆነ እንመረምረው ዘንድ አይቻለንም፡፡ ነቢዩ ኢሳይያስ እንኳን “ድንግል ትፀንሳለች ወንድ ልጅም ትወልዳለች” አለን እንጂ እንዴት እንደሚወለድ አልነገረንም /ኢሳ.7፡14፣ ጀሮም/፡፡ ከሁለት አካል አንድ አካል፣ ያለመጠፋፋት፣ ያለመለወጥ፣ ያለመመለስ፣ ያለመቀላቀል፣ ያለ ኅድረት፣ ያለ ትድምርት ይልቁንም በተዓቅቦ እንደተወሐደ ግን እናውቃለን /ቅ.ቄርሎስ/፡፡ በልቡናችን ያለ ቃል ከድምጻችን ጋር ተዋሕዶ እንደሚገለጥ ሁሉ አካላዊ ቃልም ሥጋን ተዋሕዶ እንደ ተገለጠ እናውቃለን፡፡ ነገር ግን የእኛ ቃል ከድምጻችን ጋር ይዋሐዳል እንጂ ወደ ድምጽነት አይቀየርም፤ አካላዊ ቃልም ከሥጋ ጋር እንደተዋሐደ እንጂ ወደ ሥጋነት እንዳልተለወጠ እናውቃለን /አውግስጢኖስ/፡፡ 

“ይህ ሁሉ ግን ለምን ሆነ?” ብለን ስንጠይቅም በሰው ልጆች ላይ ነግሦ የነበረው ሞትና እርሱን ተከትሎ የሚመጣው መፍረስና መበስበስ የሚነቀለው በሞት ብቻ እንደ ሆነ እንገነዘባለን /ዕብ.9፡22/፡፡ ይህንን ማድረግ የሚችል ፍጡር ደግሞ ፈጽሞ አልተገኘም /ኢሳ.59፡16/፡፡ ስለዚህ እግዚአብሔር ራሱ በመለኰታዊ ባሕርይው ስለማይሞት ሞት የሚስማማውን የእኛን ደካማ ሥጋ ነሣና ሞትን በትንሣኤው ገደለው (N.B.፡- ክርስቶስ የነሣው ሥጋ ከመለኰት ጋር ከመዋሐዱ በፊት ሀልዎት-Existence የለውም)፡፡ የተዋሐደውን ሥጋዉም ከበደል ንጹሕ የሆነ መሥዋዕት አድርጎ በማቅረብና ራሱን ለሞት አሳልፎ በመስጠት ሞትን ከወገኖቹ አስወገደ /ኤፌ.5፡2፣ ቅ.አትናቴዎስ/፡፡ በአዳም ምክንያት ያገኘን ድቀትም ፈወሰልን /ቅ.ኤፍሬም/፡፡ (ማስታወሻ፡- በኦርቶዶክስ አስተምህሮ “ጥንተ አብሶ- Original Sin” አይባልም /ይህ የካቶሊክ አስተምህሮ ነውና/፤ ይልቁንም “የባሕርይ መጐሳቆል፣ ድቀት- Failure of Nature” ነው የሚባለው /ቅ.አትናቴዎስ/)፡፡ ብረት በእሳት ውስጥ ብንጥደው እሳቱን አይጠቀልለውም፤ ነገር ግን ብረቱ የእሳቱን ባሕርይ ለራሱ ገንዘብ ያደርጋል፡፡ እሳቱ መጠኑ አይቀንስም፤ ነገር ግን ብረቱ የእሳቱን ባሕርይ ለራሱ ባሕርይ ያደርጋል፡፡ አካላዊ ቃልም ከመለኰታዊ ምልዓቱ ሳይወሰን ሥጋ ሆነ፡፡ በምልዓቱ ያልተለየውን ምድር ሰው ሆኖ ጎበኘው፡፡ የነሣው ሥጋም የመለኰትን ባሕርይ ለራሱ ገንዘብ አደረገ፤ በተዋሕዶም የባሕርይ አምላክ ሆነ፡፡ እንግዲያስ ፀሐይ በተገለጠች ጊዜ ጨለማና ሌሊት እንደሚወገዱ ሁሉ ፀሐየ ጽድቅ ኢየሱስ ክርስቶስም ከእኛ ጋር ተዋሕዶ የነበረውን ሞት ይገድል ዘንድ ከኃጢአት በቀር የእኛን ደካማ ባሕርይ በሙሉ ገንዘብ እንዳደረገ እናስተውል /ዕብ.2፡14-15፣ ቅ.ባስልዮስ/፡፡ ወንጌላዊው አስቀድሞ ቀዳማዊነቱን ከነገረን በኋላ አሁን ደግሞ እውነተኛው ብርሃን ወደ ቀደመ ክብራችን ይመልሰን ዘንድ ሥጋ እንደለበሰ የሚነግረን ለዚሁ እንደሆነ ልብ እንበል፡፡ የሰው ልጅ ሕያዊት የሆነች ነፍስና ሟች የሆነች ሥጋ አሉት፡፡ መጀመርያ ሲፈጠር ሞት የሚስማማው ባሕርይ ነበረው፡፡ በኋላም ፈጣሪ የሕይወትን እስትንፋስ “እፍ” ስላለበት የእግዚአብሔርን ሕይወት (ኢመዋቲነትን- Immortality) ተካፋይ ሆነ /ዘፍ.2፡7/፡፡ የተሰጠውን ትእዛዝ ሲተላለፍ ግን “አፈር ነህና…” ተብሎ ተቀጣ፤ አልተረገመም /ዘፍ.3፡19/፡፡ ነገር ግን ይህ ቅጣት በነፍስ ላይ የተነገረ አልነበረም ማለትም ነፍስ መበስበስን ታይ ዘንድ አልተቀጣችም /ቅ.ቄርሎስ/፡፡ ስለዚህ ሕያውና የማይሞት ቃል የሚሞት ሥጋን ለበሰ፤ ያንን የሚሞት ሥጋም የማይሞት አደረገው፡፡ ይህ የማይጠፋ ኃይል የሚጠፋ ሥጋን ለበሰ፤ ያንን የሚጠፋ ሥጋም የማይጠፋና የሚናገር አደረገው /አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ/፡፡ አማልክት ዘበጸጋ እንሆን ዘንድ የእግዚአብሔር ልጅ የሰው ልጅ ሆነ፤ ከማይታየው እግዚአብሔር እንወለድ ዘንድ ከሚታየው ባሕርያችን ተወለደ፤ ዘላለማውያን እንሆን ዘንድ ሟች ባሕርያችንን ነሣ፤ ለሞት ይኸውም የመስቀል ሞት እንኳ የታዘዘ ሆነ፤ መዋቲ ሥጋችንን ተዋሕዶ በመገለጥ በኢመዋቲነቱ መዋቲነትን አጠፋልን /ፊል.2፡8፣ ቅ.አትናቴዎስ/፡፡ የእርሱ የሆነውን ሳይተው የእኛ የሆነውን ተዋሐደ፤ የእኛ ደካማ ባሕርይ ከፍ ከፍ ያደርግ ዘንድ የእርሱ ባሕርይ ሳይጐድል መጣ /ታላቁ ጐርጐርዮስ/፡፡ 

FeedBurner FeedCount