Tuesday, July 3, 2018

ኦርቶዶክሳዊ የሕፃናት አስተዳደግ



ገብረ እግዚአብሔር ኪደ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሰኔ 26 ቀን 2010 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን !

 ማስታወሻ! ይህ ጽሑፍ ለሥልጠና ተብሎ በ “Power Point” ከተዘጋጀ ማስታወሻ እንደ ወረደ የቀረበ ስለ ኾነ በየንኡስ ርእሱ የቀረቡ አሳቦች በዝርዝር የቀረቡ አይደለም፡፡ ኾኖም ግን ዋናውንና ጠቋሚውን ብዬ ያሰብሁትን አሳብ ስላስቀመጥሁ አንባብያን ይህን መነሻ አድርገው እንደ ንባባቸውና ዕውቀታቸው እንደ ልምዳቸውም ሊያስፋፉት ይችላሉ !

 መግቢያ !
   ሕፃናትን ኦርቶዶክሳዊ አድርጎ ለማሳደግ መጀመሪያ ወላጆች ኦርቶዶክሳውያን መኾን አለባቸው፡፡
      ስለዚህ ስለ ሕፃናት ስናስብ ገና ከትዳር አጋራችን አመራረጥ መጀመር አለብን፡፡
      ምንጩ ከደፈረሰ ወንዙ ይደፈርሳልና፡፡
      ጌታችንም ሲናገር፡- “ከእሾኽ ወይን ከኩርንችትስ በለስ ይለቀማልን?” ብል (ማቴ.7፡16)፡፡
      ሐዋርያውም፡- “ሰው የሚዘራውን ኹሉ ያንኑ ደግሞ ያጭዳል” ብል (ገላ.6፡7)፡፡
      ስለዚህ የምንዘራውን ዘር ማስተካከል የግድ አስፈላጊ ነው፡፡
በመኾኑም፡-

FeedBurner FeedCount