Monday, September 9, 2019

የእነ ቀሲስ በላይ ጥያቄ ታሪካዊ ባለቤቱ ማን ነው?


በመምህር ብርሃኑ አድማስ
(ከመጽሓፈ ገጹ የተወሰደ)
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ጳጉሜን 04 / 2011 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤
አቤቱ እውነትና መንገድ ሕይወትም የሆንከው ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ስለእውነትና ስለ ጽድቅ ስለሰላምና ስለአንድነት፤ ስለመግባባትና በስምህ አንድ ስለመሆን ብቻ እመሰክር ዘንድ አንተ በምታውቃቸው በጽኑ ወዳጆችህና ስምህን ተሸክመው ዐለምን በዞሩ በቅዱሳንህ ስም እማጸንሃለሁ፡፡ ልዩነት፣ ሥጋዊ ጥቅም፣ ዝናና የበላይነት ስሜት ወደ ማንኛችንም ልጆችህ እንዳይመጣ ትጠበቀንም ዘንድ ኃጢአተኛው ባሪያህ በእውነት አለምንሃለሁ፡፡ አቤቱ በዙሪያችን የከበበውን ጨለማ አርቅ፤ ብርሃንህንም ግለጽልን፤ ስለእውነትና በእውነት ብቻ እንድናገርም ርዳን፡፡ አቤቱ በጠላታችን በዲያብሎስ አንናቅ፤ ይልቁንም ስለ ስምህ አንድ መሆንንና እርሱን መርገጥን ስጠን፤ በቅዱሳን ሁሉ ጸሎትና ከሁሉም በላይ በምትሆን በባሕርያችን መመኪያ በእናትህ በቅድስት ድንግል ማርያም ጽኑ አማላጅነት፤ አሜን፡፡

የአንድ ፓስተር ኑዛዜ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ወደ ሥልጣን ከመምጣታቸው በፊት በሀገሪቱ የነበረው ሽኩቻና ውጥረት እንዲሁም የሕዝቡ ጭንቀት ያሳሰባቸው ኢትዮጵያውያን ብዙ ነበሩ፡፡ ብዙዎች መፍትሔ የመሰላቸውን ከማድረግ ወደ ኋላ እንዳላሉ የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው፡፡ በወቅቱ ለመፍትሔ ይሯሯጡ ከነበሩት አካላት አንድ የሽማግሌዎች ቡድን ለመመሥረትና ባለሥልጣናትን በማናገር ወደ መግባባትና ሰላም ለማምጣት ሕብረ ብሔርና ሕብረ ሃይማትን ታሳቢ ያደረገ የሀገር ሽማግሌዎች ቡድን ማሰባሰብ ይጀመራል፡፡ በዚህ ሒደት ውስጥ ከኮሚቴዎቹ ሁለቱ እገዛ እንዳደርግ ሲያወያዩኝ የነገሩኝ ሽማግሌዎችን ሲያናግሩ ከገጠማቸውና ካስገረማቸው ታሪክ አንዱ የሚከተለው ነበር፡፡

Wednesday, September 4, 2019

ከገጠመን ችግር ለመውጣት በፍጥነት ልናደርገው የሚገባን ምንድን ነው?

በመምህር ብርሃኑ አድማስ
(ከመጽሐፈ ገጹ የተወሰደ)
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ነሐሴ 29 ቀን 2011 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡፡

ባለፉት ስምንት ዐመታት (ከቀድሞው ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ እና ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ዕረፍት) ወዲህ ኢትዮጵያ ባልተቋረጠ የለውጥ፣ የውዝግብና የነውጥ ሂደት ውስጥ ትገኛለች፡፡ ሁለቱም ታላላቅ መሪዎች ያረፉት በዘመነ ዮሐንስ ማጠቃለያ ወር ላይ ነበር፡፡ የእነርሱን ዕረፍት ተከትሎ እንዳሁኑ ጎልቶ ባይነገርላቸውም ብዙ ለውጦችም ነውጦችም በተከታዮች ዐመታት ውስጥ ነበሩ፡፡ ከዐራት ዐመታት በኋላ ልክ በዘመነ ዮሐንስ ደግሞ አሁን ላለንበት ለውጥም እንበለው ምስቅልቅል የዳረገን አብዮት ተቀሰቀሰ፡፡ አሁን ባለቤቱ እኔ ነኝ እኔ ነኝ የሚባልለት ሕዝባዊ ጫናን መሣሪያ ያደረገ (ከየት እንደሆነ ግን ከግምት በቀር ብዙዎቻችን በትክክል የማናውቀው) ለውጥ ተፈጠረ፡፡ አራቱን ዐመታትም የማንጠበቃቸውና ሊተነበዩ የማይችሉ ተከታታይ ለውጦች ከጥፋቶችና ምስቅልቅሎች ጋር በሀገራችን ተከሰቱ፡፡ ሁኔታዎቹም ለከፊሉ ደስታ ለከፊሉም ሐዘን የሆኑበት ብዙም ሳይቆይ ደግሞ ደስታና ሐዘን በፍጥነት የተፈራረቁበት ሆነ፡፡ እንዲህ ያሉ ክስተቶች ሳያቋርጡ ያለፉበት የዐራት ዐመታት አንድ የለውጥ ወቅት ሊፈጸም ሳምንታት ብቻ ቀርተውታል፡፡

Wednesday, August 21, 2019

ድንግል ማርያም ተነሥታለች!


በዲ/ን ኄኖክ ኃይሌ
(ከመጽሐፈ ገጹ የተወሰደ)
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ነሐሴ 14 ቀን 2011 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በልጅዋ ፈቃድ ከሞት መነሣት ኦርቶዶክውያን አባቶች ሲያስተምሩ ከመጽሐፍ ቅዱስ የሚጠቅሱት ማስረጃ በመዝ. 1318 ላይ ያለውን ‹‹አቤቱ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ አንተና የመቅደስህ ታቦት›› የሚለውን ቃል ነው፡፡ ይህንን ጥቅስ ከድንግል ማርያም ትንሣኤ ጋር አያይዞ መጥቀስ አሁን የተጀመረ ነገር ሳይሆን ብዙ ክፍለ ዘመናትን ያስቆጠረ ነገር ነው፡፡ ሠላሳ ሦስተኛው የእስክንድርያ ፓትርያርክ ቅዱስ ቴዎዶስዮስ ከእርሱ ቀድመው የተነሡ አበው ያስተላለፉለትን የእመቤታችንን ዕረፍትና ትንሣኤ ታሪክ የዛሬ ከአንድ ሺህ አምስት መቶ ዓመታት በፊት በጻፈው ድርሳን ላይ በነገረ ማርያም ሊቃውንት ዘንድ Doctor of Dormition በመባል የሚታወቀው ሊቁ ዮሐንስ ዘደማስቆ ሐዋርያውያን አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ በድርሳኖቻቸው ላይ ስለ ድንግል ማርያም ትንሣኤ ባነሡና በዓለ ዕርገትዋን ባከበሩ ቁጥር የሚያነቡት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ‹‹አቤቱ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ አንተና የመቅደስህ ታቦት›› የሚለውን የዳዊት መዝሙር ነው፡፡ በእርግጥ ይህንን ቃል ከድንግል ማርያም ጋር ምን ያገናኘዋል? ‹ማርያም ተነሣችየሚል ነገር አለውን? የሚለውን ጥያቄ በዚህች አጭር ጽሑፍ እንመለከታለን፡፡ ወደዚህ ጉዳይ ከመግባታችን በፊት ግን አንድ ቁምነገርን እናስቀድም፡፡

FeedBurner FeedCount