Showing posts with label ክርስቲያናዊ ሕይወት. Show all posts
Showing posts with label ክርስቲያናዊ ሕይወት. Show all posts

Tuesday, July 3, 2018

ኦርቶዶክሳዊ የሕፃናት አስተዳደግ



ገብረ እግዚአብሔር ኪደ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሰኔ 26 ቀን 2010 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን !

 ማስታወሻ! ይህ ጽሑፍ ለሥልጠና ተብሎ በ “Power Point” ከተዘጋጀ ማስታወሻ እንደ ወረደ የቀረበ ስለ ኾነ በየንኡስ ርእሱ የቀረቡ አሳቦች በዝርዝር የቀረቡ አይደለም፡፡ ኾኖም ግን ዋናውንና ጠቋሚውን ብዬ ያሰብሁትን አሳብ ስላስቀመጥሁ አንባብያን ይህን መነሻ አድርገው እንደ ንባባቸውና ዕውቀታቸው እንደ ልምዳቸውም ሊያስፋፉት ይችላሉ !

 መግቢያ !
   ሕፃናትን ኦርቶዶክሳዊ አድርጎ ለማሳደግ መጀመሪያ ወላጆች ኦርቶዶክሳውያን መኾን አለባቸው፡፡
      ስለዚህ ስለ ሕፃናት ስናስብ ገና ከትዳር አጋራችን አመራረጥ መጀመር አለብን፡፡
      ምንጩ ከደፈረሰ ወንዙ ይደፈርሳልና፡፡
      ጌታችንም ሲናገር፡- “ከእሾኽ ወይን ከኩርንችትስ በለስ ይለቀማልን?” ብል (ማቴ.7፡16)፡፡
      ሐዋርያውም፡- “ሰው የሚዘራውን ኹሉ ያንኑ ደግሞ ያጭዳል” ብል (ገላ.6፡7)፡፡
      ስለዚህ የምንዘራውን ዘር ማስተካከል የግድ አስፈላጊ ነው፡፡
በመኾኑም፡-

Monday, June 11, 2018

ምሥጢራትን የመሳተፍ ሕይወት

በ ገብረ እግዚአብሔር ኪደ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሰኔ 04 ቀን 2010 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! 
 
የኦርቶዶክሳዊ ሕይወት ዋና ዓላማውና ግቡ ምእመናን እግዚአብሔርን እንዲመስሉ፣ በቅድስና ላይ ቅድስና፥ በክብር ላይ ክብር፥ በጸጋ ላይ ጸጋ እየጨመሩ እየተመነደጉም እንዲኼዱ ነው፡፡ እግዚአብሔር ደግሞ፡- “ለክብርህ ከፍተኛነት ፍጻሜ የለውም” እንዲል፥ ቅድስናው፣ ቸርነቱ፣ መልካምነቱ፣ ክብሩ ወሰን ድንበር ስለሌለው እርሱን መምሰልም ወሰን፣ ድንበር፣ ልክ የለውም፡፡ በዚህ ዓለም ብቻ ሳይኾን በወዲያኛውም ዓለም የማይቋረጥ ምንድግና ነው፡፡ ስለዚህ የኦርቶዶክሳዊ ሕይወት ዋና ዓላማና ግብ እግዚአብሔርን መምሰሉ ብቻ ሳይኾን ይህ ራሱ የማይቋረጥ እድገትም ነው፡፡ ከአንዱ ክብር ዓይን ወዳላየችው፣ ጆሮ ወዳልሰማችው፣ የሰውም ልብ ወዳላሰበው ወደ ሌላ ክብር መወለጥ ነው፡፡ 

Thursday, August 17, 2017

“እስክመጣ ድረስ በማንበብ ተጠንቀቅ” (1ኛ ጢሞ.4፡13)፡፡



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ነሐሴ 11 ቀን 2009 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
እንደ መንደርደሪያ
ኃይለ ቃሉን የተናገረው በመንፈሳዊው ትምህርት ከሕግ መምህሩ ከገማልያል፣ በዚህ ዓለም ትምህርት ደግሞ በዘመኑ እጅግ ታዋቂ ከነበረው የተርሴስ ዩኒቨርሲቲ በእጅግ ከፍተኛ ማዕረግ የተመረቀው ንዑድ ክቡር የሚኾን ጳውሎስ ነው፡፡ የተናገረው ደግሞ በመንፈስ ለወለደው ልጁ ለሊቀ ጳጳሱ ለቅዱስ ጢሞቴዎስ ነው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ለቅዱስ ጢሞቴዎስ፡- “እስክመጣ ድረስ በማንበብ ተጠንቀቅ፤ በማንበብ ተወስነህ ኑር” በማለት መንፈሳውያን መጻሕፍትን እንዲያነብ ሲመክረውም ምክንያቱን ነግሮታል፤ እንዲህ ሲል፡- “ይህን ብታደርግ ራስህንም የሚሰሙህንም ታድናለህ” (1ኛ ጢሞ.4፡16)፡፡
ስለዚህ መንፈሳዊ ንባብ ማለት ራሳችንንም የሚሰሙንንም ለማዳን - አስተውሉ! ለማዳን - መጽሐፍ ቅዱስን ጨምሮ የአበው ድርሳናትን፣ ትርጓሜያትን፣ ምክሮችን፣ ገድሎችን፣ ታሪኮችን ማንበብ ማለት ነው፡፡ ስለዚህ የማንበብ ግቡ እኛ ራሳችን እግዚአብሔርን ወደ መምሰል እንድናድግ ሌሎችንም ወደዚህ ምንድግና እንዲመጡ ማድረግ ነው ማለት ነው፡፡ ንባብ ብቻ ሳይኾን የማንኛውም መንፈሳዊ ግብር ዓላማም ከእግዚአብሔር ጋር ኅብረትና አንድነት መፍጠር ነው፡፡
ከላይ ባነሣነው የቅዱስ ጳውሎስ ቃል እንደምንመለከተው አንድ ኦርቶዶክሳዊ ኹልጊዜ በመደበኛነት ሊያነብ እንደሚገባው ያስረዳል፡፡ ጢሞቴዎስ ጳጳስ ነው፡፡ ቢኾንም ግን ማንበብ - ያውም ኹልጊዜ - መጻሕፍትን መመልከት እንዳለበት ተመከረ! ቅዱስ ጢሞቴዎስ ከሴት አያቱና ከእናቱ ከልጅነቱ አንሥቶ ቅዱሳት መጻሕፍትን ሲያነብ ያደገ ነው (2ኛ ጢሞ.3፡14-15)፡፡ አሁንም ቅዱስ ጳውሎስ ተቀብሎ ይበቃሃል ሳይኾን “በማንበብ ተጠንቀቅ” አለው፡፡

Friday, August 4, 2017

ዓላማውን ያልሳተ ሕይወት

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐምሌ 28 ቀን 2009 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
አንድ እኁ (ወንድም) ወደ አባ ሄላርዮን መጣና፡- “አንድ ሰው ሌሎች እርሱን የሚመስሉ አኀው ወደ ዓለም ተመልሰው ሲወድቁ አይቶ እንደ እነርሱ ላለመውደቅ ምን ማድረግ አለበት?” ሲል ጠየቃቸው፡፡ እርሳቸውም እንዲህ አሉት፡- “አንድ ታሪክ ልንገርህ፡፡ ጥንቸሎችን ለማደ’ን የሚሮጡ ውሾችን አስብ፡፡ ከእነዚህ ውሾች መካከል አንዱ በሩቅ ያለችን ጥንቸል ተመለከታት፡፡ ወዲያውም እርሷን ለመያዝ ሩጫውን ጀመረ፡፡ አብረዉት የነበሩ ውሾችም አንዱ ሲሮጥ አይተው ጥንቸሊቱን ሳያዩዋት ተከትለውት ሮጡ፡፡ ለጊዜው አብረዉት ሮጡ፡፡ ሲደክማቸው ግን ሩጫውን አቆሙ፡፡ ማቆም ብቻ ሳይኾን እያዘገሙ ቅድም ወደ ነበሩበት ስፍራ ተመለሱ፡፡ ያ አንዱ ውሻ ግን ሩጫውን ቀጠለ፡፡

Monday, March 16, 2015

ወደ እግዚአብሔር ለመድረስ (ደረጃ አራት)





በዲ/ን ሳምሶን ወርቁ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ማክሰኞ መጋቢት 8 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
መታዘዝ
የተከበራችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች፥ የመንግሥተ እግዚአብሔር ተጓዦች እንዴት ሰነበታችሁ? አራተኛውን የመንፈሳዊ ሕይወት ደረጃ እነሆ በምናባችን ዛሬ መመልከታንን እንቀጥላለን፡፡ አስቀድመን የመጀመሪያውን የመንፈሳዊ ሕይወት ደረጃ ጀርባችን ለዓለም በመስጠት ጀምረን፣ ሁለተኛውን የመንፈሳዊ ሕይወት ደረጃ ከዓለማዊ መሻት መለየትን አስከትለን፣ በሦስተኛው የመንፈሳዊ ሕይወት ደረጃ የሆነውን እንደ እንግዳ መኖርን በባለፉት ጊዜያት ተመልክተናል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ዘላዕለይ አራተኛውን የመንፈሳዊ ሕይወት ደረጃ መታዘዝ ሲል ይገልጸዋል፡፡ ይህንንም ሲገልጽ መታዘዝ ማለት የእኔ የምንለውን ሐሳብ፣ ፈቃድ በመተው በምትኩ እኛ ራሳችንን አስገዝተንለታል ለምንለው ለእግዚአብሔር ፈቃድ በመታዘዝ መኖር ማለት ነው፡፡

Thursday, December 25, 2014

ወደ እግዚአብሔር ለመድረስ (ደረጃ ሦስት)



በዲ/ን ሳምሶን ወርቁ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐሙስ ታኅሳስ 16 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!


“እንደ እንግዳ መኖር”
 የተከበራችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች የመንግሥተ እግዚአብሔር ተጓዦች እንዴት ሰነበታችሁ? እነሆ ሦስተኛውን የመንፈሳዊ ሕይወት ደረጃ በምናባችን ዛሬ እንመለከታለን፡፡ አስቀድመን የመጀመሪያውን የመንፈሳዊ ሕይወት ደረጃ ጀርባችንን ለዓለም በመስጠት ጀምረናል፡፡ በመንገዱ ያሰበበት ለመድስ የሚጓዝ አሽከርካሪ በመንገድ እንዳይቀር በየደረሰበት ከተማ ነዳጅ እንደሚሞላ እኛም ተስፋ ወደምናደርጋት መንግሥተ እግዚአብሔር እስክንደርስ ድረስ በየደረጃዎቹ ላይ የምናገኛቸውን የቃለ እግዚአብሔር ስንቅ እየቋጠርን እንጓዛለን፡፡ በባለፈው ጽሑፍ “ከዓለማዊ መሻት መለየት” ሁለተኛውን የመንፈሳዊ ሕይወት ደረጃ ተመልክተናል፡፡ ከዓለማዊ መሻት መለየት በዓለም ካለው አላፊ ጠፊ ከሆነው ከገንዘብ ከሥልጣን ከዕውቀት ፍቅር ተለይተን፤ በምድር ላይ ስንኖር አለን የምንለው ነገር ሁሉ ከእኛ እንዳልሆነ አውቀን፤ ከራስ ወዳድነት ርቀንና ከውዳሴ ከንቱ ተለይተን መኖር ማለት መሆኑን ተመልክተናል፡፡

Thursday, December 4, 2014

ወደ እግዚአብሔር ለመድረስ (ደረጃ ሁለት)



በዲ/ን ሳምሶን ወርቁ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐሙስ ኅዳር 25 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ከዓለማዊ መሻት መለየት
 የተከበራችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እንዴት ሰነበታችሁ? ወደ እግዚአብሔር ለመድረስ በሚለው ጽሁፍ ወደ እግዚአብሔር ለመድረስ  በያዕቆብ ምናባዊ መሰላል ደረጃ ለዓለም ጀርባ መስጠት የመጀመሪያ መሆኑን ተመልክተናል፡፡ በዚህ ያዕቆብ በራዕይ በተመለከተው ምናባዊ መሰላል ላይ እግራችን መውጣት ጀምሯል፡፡ አሁን ለዓለም ጀርባ ስለሰጠን አይኖቻቸን ወደ እግዚአብሔር የሚመለከቱ ጆሮዎቻችን ድምጹን ለመስማት የሚቀኑ መሆን ይጀምራሉ፡፡ ምንያቱም ለዓለም ጀርባ ስለሰጠን ኃጢአትን መጥላት፣ የእግዚአብሔርን ፍቅሩንና ቸርነቱን መረዳት ጀምረናል፡፡ አሁን በእውነት እኛ ወደ እግዚአብሔር በማደርገው ጉዞ እንደርስ ይሆን የሚል ስጋት አይገባንም ምክንያቱም እኛ እስከፈቀድን ድረስ ከድካማችን ሊያሳርፈን ከወደቅንበት የሚያነሳን አምላክ ሊረዳን እንደቀረበ አውቀን ተረድተናልና፡፡ አሁን ጥያቄው እንዴት በመንገዳችን ጸንተን እንጓዝ የሚል ነው?

Wednesday, November 12, 2014

ወደ እግዚአብሔር ለመድረስ (ደረጃ አንድ)

በዲ/ ሳምሶን ወርቁ

  (መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐሙስ ኅዳር ቀን፣ ፳፻፯ ..)- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
 
ለዓለም ጀርባችንን እንስጥ

 እግዚአብሔር ለሰው እውቀትና ነጻ ፈቃድ ሰጥቶ አክብሮ ፈጠረው፡፡ አንዳንዶች ነጻ ፈቃዳቸውን ተጠቅመው እውነተኛ የእግዚአብሔር ወዳጅ ሆኑ፤ አንዳንዶች በስንፍናቸው ነጻ ፈቃዳቸውን ተጠቅመው ልግመኛ ክፉ አገልጋይ ሆኑ፡፡
ቅዱስ ዮሐንስእኔ ከየትኛው ነው የምመደበው? ከእውነተኞቹ አገልጋዮች ወይስ ከሀሰተኞቹ?” ብለን ራሳችንን እንጠይቅ ይለናል፡፡ የተጠመቀ ሁሉ የእግዚአብሔር መንግሥት ወራሽ አይደለም፣በጠባቡ ደጅ የሚገባ ሁሉ በጽናት ላይጓዝ ይችላል (ማቴ 713)፡፡ መጠመቃችን በራሱ ብቻውን ወደ መንግሥተ ሰማያት ለመግባታችን ዋስትና አይደለም፡፡ ጥምቀት (ከኃጢያትና በኃጢአት ከመጣብን ፍዳ መዳን) ወደ ድኅነት የመግቢያ በር እንጂ ብቻውን የድኅነት መደምደሚያ አይደለም፡፡ መንፈሳዊ ሕይወትን መጀመራችን በራሱ ፍጻሜአችንን መልካም ያደርጋል ለማለት አያስችለንም፡፡  ይህ ማለት ያመነ ሊክድ ያወቀ ሊጠራጠር እና በጎ አገልጋይ ወደ ክፉ ባሪያነት ሊለወጥ የሚችልበት እድል ዘወትር አለ፡፡ አንዳንዶች በመጠመቃቸው ብቻ እንደሚድኑ የሚያስቡ አሉ፡፡ ነገር ግን ጥምቀት ብቻውን ከእግዚአብሔር የተገባልንን ቃልኪዳን አያስጠብቅልንም፡፡ ስለዚህ የመንፈሳዊ ሕይወታችንን ትክክለኛ አቅጣጫ ልንመለከት ልንመረምር ይገባል፡፡ማንም ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማይ አይገባም የአባቴን ፈቃድ የሚፈጽም እንጂእንዲል (ማቴ 721)፡፡

Wednesday, November 5, 2014

አምስቱ ስጦታዎች

በቀሲስ ፋሲል ታደሰ




(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ጥቅምት 27 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!! 

ሥርዓተ አምልኮ ከሚገለጥበት መንገድ አንዱ ስጦታ ነው፡፡ የሰው ልጅ ከራሱ የኾነ አንዳች የለውም፤ በጎ የኾነው ኹሉ ከፈጣሬ ዓለማት ከእግዚአብሔር ያገኘው ነው፡፡ በመኾኑም ፈጣሪያችን መስጠትን እንዳስተማረን ኹሉ እኛም ተገዥነታችንን ከምንገልጥበት አንዱ ከርሱ የተቀበልነውን በፈቃደኝነት በደስታ በመስጠት ነው፡፡ ነቢዩ ዳዊት ይኽን ሲያስረዳ “ኹ ከአንተ ዘንድ ነውና፡ ከእጅህ የተቀበልነውን ሰጥተንሃልና ይኽን ያኽል ልናቀርብልህ የቻልን ማነን? በፈቃዴ ይህን አቅርቤአለሁበማለት ከእግዚአብሔር ያገኘውን ሀብት በደስታ በፈቃዱ ለቤተ መቅደስ ሥራ እንዲውል መስጠቱን በመግለጽ ስለ ስጦታ ጽፏል /1ዜና 29÷9-16/፡፡

FeedBurner FeedCount