Showing posts with label ቅድስት ዘረቡዕ. Show all posts
Showing posts with label ቅድስት ዘረቡዕ. Show all posts

Tuesday, March 4, 2014

ቅድስት ዘረቡዕ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 25 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ
ጸልዩ እምቅድመ ንባበ ዝንቱ ክርታስ
 ‹‹ ሐዋዘ ብርሃነ እግዚኦ ነግሐ ነቂሐነ እምንዋም ንጊሣ ለቤተክርስቲያን ኃበ የኃድር ብዕለ ስብሐቲሑ ንስአል እም ሐቤሁ ረድኤተ ወሕይወተ ኩሉ ዘጌሰ ወመጽአ ኢይጻሙ - አቤቱ ያማረ ብርሐንን ስጠን፤ ነጋ ከእንቅልፋችንም ነቃን፤ የምስጋናው ሐብት ወደሚያድርባት ወደ ቤተ-ክርስቲያን እንገስግስ፤ የሁሉ ህይወት ከሚሆን ከእርሱም እርዳታን እንለምን፤ ወደ እርሷ የገሰገሰ የመጣም አይደክምም፡፡›› ቀኑን ሰላም አውሎ ሌሊቱን ሰላም አሳድሮ ትናንት የነበሩት በሌሉባት ዛሬ ነገን ተስፋ እናደርግ ዘንድ ጠብቆ ለዚህ ያደረሰንን አምላካችንን አመስግነን ቅዱስ ያሬድ እንደሚነግረን ስለማይነገር ስጦታው የምንከፍለው የሌለን በቤቱ በመገስገስ ህይወትን ለምነን አመስግነን በደስታ እንኖር ዘንድ አምላኬ እና መድኃኒቴ በሚሆን በክርስቶስ የመድኃኒቴ ዘውድ በሚሆን በአባቱ የቅድስናዬ መገኛ በሚሆን መንፈስ ቅዱስ በከበረች እናቴ የገነት ሙሽራ ድንግል ማርያም እንዲሁም ሰላማቸው በበዛ በማኅበረ ጻድቃን ስም ሁሉ ሰላማችሁ ይብዛ እላለሁ፡፡

FeedBurner FeedCount