Showing posts with label ትንቢተ ዮናስ - ክፍል ኹለት. Show all posts
Showing posts with label ትንቢተ ዮናስ - ክፍል ኹለት. Show all posts

Monday, February 22, 2016

ትንቢተ ዮናስ - ክፍል ኹለት



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 14 ቀን 2008 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!


ምዕራፍ ኹለት


ዮናስ ወደ ባሕሩ ተጣለ፡፡ ኾኖም ይሞት ዘንድ አይደለም፡፡ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነውና ይሞት ዘንድ አይደለም፡፡ እግዚአብሔር የነነዌን ሰዎች እንዲያድናቸው ወዷልና ዮናስ የተጣለው እንዲሞት አይደለም፡፡ በሰዎች እይታ ዮናስ ለዚህ የተገባ አይደለም ሊባል ይችላል፡፡ በእግዚአብሔር እይታ ግን የተገባ ነው፡፡ አሁንም እግዚአብሔር ይወዷል፤ ልጄ ይሏል፤ የእኔ ነቢይ ብሎ ይጠራዋል፡፡ ምንም እንኳን ለወገኖቹ ለእስራኤል አዝኖ አልታዘዝ ቢልም፣ አለመታዘዙ ወደ ሌላ ኃጢአት እንዲገባ ቢያደርገውም አሁንም እግዚአብሔር ዮናስን ይፈልገዋል፡፡ ነነዌን ያድናታል፡፡ እግዚአብሔር ትዕግሥተኛ ነው፡፡ እንደ እኛ ለፍርድ አይቸኩልም፡፡ ለመቅጣት አይቸኩልም፡፡ በወደቁ ልጆቹ ፈጥኖ አይፈርድም፡፡ ለፍርድ የምንቸኩለው እኛ ነን፡፡ ከወደቁ ሰዎች ጋር ያለን ግንኝነት ፈጥነን የምናቋርጥ እኛ ነን፡፡ እርሱ እግዚአብሔር ግን እንዲህ አይደለም፡፡ እግዚአብሔር ጠባቂ ነው፡፡ በጣም ብዙ ጊዜ ይጠብቃል፡፡ እግዚአብሔር እንዲህ በትዕግሥት የሚጠብቀን ባይኾን እስከ አሁን ማን ይቆይ ነበር? ማን ቀና ብሎ ይሄዳል? የቆየነው እንጀራ ብቻ በልተን አይደለም፤ መድኃኒት ውጠንም አይደለም፡፡ እግዚአብሔር ስለጠበቀን እንጂ፡፡ ስንበድል ዕድሜ ለንስሐ ሰጥቶን እንጂ፡፡ ስንቶቻችን መርዝ በጥብጠናል? ስንቶቻችን ገመድ አንጠልጥለናል? ስንቶቻችን ስለት ስለናል? እግዚአብሔር ግን ከዚያ ጠበቀን፡፡ አሁንምልጄ! እወድሃለሁ፤ ልጄ! እወድሻለሁይለናል፡፡

FeedBurner FeedCount