Showing posts with label ለመላው ኦርቶዶክሳውያን ፦ ታላላቅ የአንድነት የስብከትና የዝማሬ ጉባኤያትን ስለማዘጋጀት - ጥቆማ. Show all posts
Showing posts with label ለመላው ኦርቶዶክሳውያን ፦ ታላላቅ የአንድነት የስብከትና የዝማሬ ጉባኤያትን ስለማዘጋጀት - ጥቆማ. Show all posts

Thursday, January 9, 2014

ለመላው ኦርቶዶክሳውያን ፦ ታላላቅ የአንድነት የስብከትና የዝማሬ ጉባኤያትን ስለማዘጋጀት - ጥቆማ



በታምራት ፍሰሓ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ጥር ፪ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- ኦርቶዶክሳዊት እምነታችን በብዙ መስክ (በቅዳሴ በማህሌት በሰአታት በሰርክ ጉባኤያት በበዓላት ዝግጅቶች) በልዩ ስርአት ወጥነት ሐዋርያዊ መሰረተ እምነቷን ለምእመናን ስታስተላልፍ ቆይታለች አሁንም በማስተላለፍ ላይ ትገኛለች፤ በቅዳሴው ለተካፈለ በማህሌቱም ለተሳተፈ በሰአታቱም ለተገኘ በሰርክ ጉባኤውም ላልቀረ ይህ እሙን ነው፡፡ ነገር ግን ስንቶቻችን በነዚህ ተገኘን? ካልተገኘንስ እንደምን እምነታችንን ልናውቅ በእምነታችንስ ልንፀና ይቻለናል?

ብዙወቻችን ደግሞ የቤተክርስቲያን ታላላቅ በዓላትን (ደመራ ጥምቀት) መሰረት በማድረግ ተገኝተን እናከብራለን ይህም በጣም ብዙ ኦርቶዶክሳዊ በአንድነት የሚገናኙባቸው ክስተቶች ቢሆኑም ነገር ግን እኒህ ልዩ በዓላት እንደመሆናቸው የራሳቸው የሆነ የአከባበር ስርአትና ይዘት ያላቸው በመሆኑ በዚህ ጊዜ ለሚገኙ ምእመናን የሚገባውን ያህል ትምህርት ሰጥተው የሚያልፉ አይደለም ይልቅስ በነዚህ በዓላት ጥቂት ከመዘመርና በዓሉን የመታዘብ ያክል ከተመለከትን በኅላ ወደቤታችንም ሆነ ወደሌሎች ጉዳዮች የምንመለስ ብዙወች ነን፡፡ ስለዚህም ኦርቶዶክሳውያን ሁሉ በአንድነት ተሰባስበን የቤተክርስቲያናችንን ስብከቷን ዝማሬዋንም ሆነ ልዩ ልዩ ሃሳቦቿን የምንረዳባቸው የምንሳተፍባቸውና የምንወያይባቸው መድረኮች የሉንም፡፡

FeedBurner FeedCount