Showing posts with label ስግደት ክፍል - 3. Show all posts
Showing posts with label ስግደት ክፍል - 3. Show all posts

Monday, April 25, 2016

ስግደት ክፍል - 3



በዲ/ን ሕሊና በለጠ ዘኆኅተ ብርሃን
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ 17 ቀን፣ 2008 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ስግደት ለመላእክት ይገባልን?
መጽሐፍ ቅዱስ ለመላእክት መስገድ እንደሚገባ ያስተምራል፡፡ በብሉይ ኪዳንም ሆነ በሐዲስ ኪዳን ሰዎች ለእግዚአብሔር መላእክት ይሰግዱ ነበር፡፡ የሚከተሉትን በማስረጃነት ማቅረብ ይቻላል፡፡
በለዓም ባልታዘዘው መንገድ ሲሔድ፣ መሔዱን እግዚአብሔር አልወደደምና የእግዚአብሔር መልአክ ሊከለክለው መጣና ከመንገዱ ቆመ፡፡ በለዓም መልአኩን ማየት ባይችልም የበለዓም አህያ ግን ከፊቷ የቆመውን መልአክ ዐይታ አልሔድም ብላ ቆመች፡፡ በለዓምም ሦስት ጊዜ ደበደባት፡፡ በመጨረሻም አህያይቱ በሰው አንደበት አናገረችው፡፡ በዚህን ጊዜ እግዚአብሔር የበለዓምን ዐይን ከፈተና መልአኩን ማየት ቻለ፡፡ ለመላእክት ስግደት ይገባልና ወዲያውም ሰገደለት፡፡ መልአኩም አልተቃወመውም፡፡እግዚአብሔርም የበለዓምን ዐይኖች ከፈተ፤ የእግዚአብሔርን መልአክ በመንገድ ላይ ቆሞ የተመዘዘም ሰይፍ በእጁ ይዞ ዐየ ሰገደም፤ በግንባሩም ወደቀ፡፡ዘኁ. 2231፡፡

FeedBurner FeedCount