Showing posts with label ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ - ክፍል ፬. Show all posts
Showing posts with label ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ - ክፍል ፬. Show all posts

Friday, May 20, 2016

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ - ክፍል ፬

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ግንቦት 12 ቀን፣ 2008 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

አባ ዮሐንስ አፈወርቅ

ከዚህ በፊት እንደገለጽነው ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ወደ ገዳም እንዳይሔድ የዘገየው በእናቱ ተማጽኖ ነው፡፡ 372 .. ግን እናቱ ስላረፈች ይጓጓለት ወደነበረው ገዳም ሔደ፡፡ የገዳሙ ስም ሲልፕዮስ ይባላል፡፡ ሲልፕዮስ እጅግ ጫካ የተሞላበት የጽሞና ሥፍራ ነው፡፡
ጰላድዮስ እንደሚነግረን ቅዱስ ዮሐንስ ወደዚህ እንደ ደረሰ አንድን አባት አገኘ፤ አባ ሲሲኮስ ይባላሉ፡፡ አራት ዓመትንም ከእርሳቸው ጋር ቆየ፡፡ በዚህ አራት ዓመት ውስጥ ከእኒህ አባት በዓት አጠገብ የራሱ የኾነ በዓት ነበረው፡፡ ሌሊቱን ሙሉ እንደዚሁም ከቀኑ አብዛኛውን ሰዓት በበዓቱ ያሳልፍ ነበር፡፡ አብዝቶ ይጸልያል፤ ቅዱሳት መጻሕፍትን ያነባል፡፡ በተለይ በዚህ ገዳም የጽሞና ሕይወት በእጅጉ ይተገበር ነበር፡፡ የሚተኛው በሳር በተጎዘጎዘ መሬት ላይ ነበር፡፡ የሚለብሰው የፍየልና የግመል ቆዳ ነው፡፡ የሚበላው በቀን አንዴ ሲኾን ዳቦ በጨው ነበር፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ይህ ኹልጊዜ ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገር የኾነው ሕይወት፡- “አዳም ከመበደሉ በፊት የነበረው ሕይወት ነውብሎ የማቴዎስ ወንጌልን ሲተረጉም 38ኛው ድርሳኑ ላይ ገልጾታል፡፡ አባ ሲሲኮስ ብዙ አምላካዊ ራዕዮችን እያዩ የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የወደፊት ታላቅነቱን ዐይተዋል፡፡

FeedBurner FeedCount