Showing posts with label ትምህርተ ሃይማኖት (ክፍል ሰባት). Show all posts
Showing posts with label ትምህርተ ሃይማኖት (ክፍል ሰባት). Show all posts

Monday, January 12, 2015

ትምህርተ ሃይማኖት (ክፍል ሰባት)

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ማግሰኞ ጥር 5 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ስለ እግዚአብሔር መኖር
 ውድ የመቅረዝ ተከታታዮች እንዴት አላችኁ? ባለፉት ስድስት ተከታታይ የመግቢያ ትምህርቶች ጠቃሚ መንፈሳዊ ግንዛቤን እንዳገኛችኁ ተስፋ እናደርጋለን፡፡ በዛሬው ትምህርታችን ደግሞ የትምህርተ ሃይማኖት መሠረት ስለኾነው ስለ እግዚአብሔር መኖር እንማማራለን፡፡ የሊድያን ልቡና የከፈተ አምላክ የእኛንም የልቡናችን ዦሮ ከፍቶ ይግለጽልን፡፡ አሜን!!!   
 ስለ እግዚአብሔር መኖር ብዙዎቻችን እናምናለን፡፡ በተለይ በኢትዮጵያ ውስጥ ስለ እግዚአብሔር መኖር የማያውቅ ማኅበረ ሰብእ ከቁጥር የሚገባ አይደለም፡፡ ነገር ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲኽ መዝሙረኛው ክቡር ዳዊት፡- “ሰነፍ በልቡ አምላክ የለም ይላል” እንዳለ /መዝ.14፡1/ አንዳንድ ሰዎች የእግዚአብሔርን መኖር ጥያቄ ማንሣታቸው አልቀረም፡፡ በተለይም የምዕራቡ ዓለም የትምህርት ሥርዓት ከተስፋፋ ወዲኽ እንዲኽ ዓይነት ጥያቄዎች በአንዳንዶቹ ዘንድ የሚመላለስ ኾኗል፡፡

FeedBurner FeedCount