Showing posts with label ትንቢተ ዮናስ - ክፍል አንድ. Show all posts
Showing posts with label ትንቢተ ዮናስ - ክፍል አንድ. Show all posts

Sunday, February 21, 2016

ትንቢተ ዮናስ - ክፍል አንድ



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 13 ቀን 2008 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
መግቢያ፡
ትንቢተ ዮናስ 46 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት አንዱ ነው፡፡ የመጽሐፉ ጸሐፊም ነቢዩ ዮናስ ይባላል፡፡ ዮናስ ማለት ርግብ፣ የዋኅ ማለት ሲኾን የነበረበትም ዘመን በዳግማዊ ኢዮርብአም ዘመነ መንግሥት /825-784 .../ ነው፡፡ በትውፊት እንደሚነገረው ዮናስ ነቢዩ ኤልያስ ከሞት ያስነሣው የሠራፕታዋ መበለት ልጅ ነው /1ነገ.1810-24/፡፡ ነቢዩ ዮናስ ምንም እንኳን የእስራኤል ነቢይ ቢኾንም ያስተማረው ከምድረ እስራኤል ውጪ ማለትም በነነዌ ስለኾነ፣ ነቢየ አሕዛብ ይባላል፡፡ ሊቃውንት እንደሚናገሩት ይህቺ ነነዌ በጤግሮስ ወንዝ ምሥራቃዊ ቆሬ፣ ከዛሬዋ የሞሱል ከተማ በተቃራኒ ከባግዳድ ሰሜን ምዕራብ 350 .. ርቀት ላይ ነበረች፡፡ የትንቢተ ዮናስ መጽሐፍ ዋና መልእክት እግዚአብሔር የእስራኤል ብቻ ሳይሆን የአሕዛብም አምላክ እንደሆነና በንስሐ ወደ እርሱ የተመለሱትን ሁሉ በምሕረት እንደሚጐበኝ ማሳየት ነው፡፡ በመሆኑም በአራት ተከታታይ ክፍል የእያንዳንዱን ምዕራፍ ትርጓሜ በተለይ ደግሞ ከሕይወታችን ጋር እያገናዘብን እንመለከተዋለን፡፡ ቅዱሳን አባቶቻችን ይህን የነነዌን ጾም ከዓቢይ ጾም ኹለት ሳምንት አስቀድመን እንድንጾመው ማድረጋቸው ያለ ምክንያት አይደለምና፡፡ በዚህ መጽሐፍ በሁዳዴ ጾም ልናከናውነውና ሊኖረን የሚገባ የንስሐና የጾም ዓይነት ምን ሊመስል እንደሚባ፣ የእግዚአብሔር ፍቅርና ጥበብ እንደምን የበዛ እንደኾነ፣ ነቢያት እንኳ ድካም እንደነበረባቸውና እንደምን እንደተነሡ እንመለከታለን፡፡ እግዚአብሔር ማስተዋሉን ያድለን፡፡

FeedBurner FeedCount