Showing posts with label ትንቢተ ዮናስ - የመጨረሻው ክፍል. Show all posts
Showing posts with label ትንቢተ ዮናስ - የመጨረሻው ክፍል. Show all posts

Wednesday, February 24, 2016

ትንቢተ ዮናስ - የመጨረሻው ክፍል



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 16 ቀን 2008 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

ምዕራፍ አራት

ሰብአ ነነዌ ስለዳኑ በሰማያት ሐሴት ኾኗል፡፡ እግዚአብሔር ደስ ተሰኝቷል፡፡ መላእክት እርስ በእርሳቸው፡- “እንኳን ደስ ያለህ! እንኳን ደስ ያላችሁ! በአንዲት ቀን ብቻ መቶ ሀያ ሺሕ የነነዌ ሰዎች ወደ እግዚአብሔር ተመልሰዋልይባባላሉ፡፡ ዮናስ ግን ፈጽሞ አዝኗል፡፡ ከአፍአ (ከውጭ) ሲታይ ዮናስ አሕዛብ ስለዳኑ የተበሳጨ ይመስላል፤ ኾኖም ግን ደጋግመን እንደተናገርን ዮናስ እንዲህ የሚያዝነው ወገኖቹ እስራኤል ከእግዚአብሔር ኅብረት መለየታቸውን አይቶ ነው፡፡ ዮናስ በሕይወት ከመኖር ይልቅ ሞትን የሚመርጠው ወገኖቹን እስራኤልን እጅግ ከመውደዱ የተነሣ ነው፡፡ ቅዱስ ጀሮም ነቢዩ ዮናስ ለምን እንዲህ ፈጽሞ እንዳዘነ ሲናገር፡- “ዮናስ እጅግ አዘነ፡፡ ኾኖም አንዳንድ ሰዎች እንደሚሉት ሰብአ ነነዌ ስለዳኑ አልነበረም፡፡ የአሕዛብ መዳን የወገኖቹ የእስራኤል መጥፋት መኾኑን ስላወቀ እንጂ፡፡ ከነቢያት ተለይቶ የወገኖቹን የእስራኤልን መጥፋት እንዲናገር በመመረጡ እንጂ፡፡ በመኾኑም ወገኖቹ እስራኤል ከሚሞቱ እርሱ ቢሞት ተመኘ፡፡ ይኸውም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የእስራኤል መጥፋት አይቶ እንዳለቀሰው ነው /ማቴ.2337/ ሐዋርያት በሥጋ የሚዛመድዋቸው ወገኖቻቸው ከክርስቶስ አንድነት ተለይተው በመቅረታቸው ስለ እነርሱ የተረገሙ እንዲኾኑ እንደጸለዩት ነው /ሮሜ.94-5/” ብሏል /St. Jerome, Commentary on the Book of Jonah, IV:1/፡፡

FeedBurner FeedCount