Showing posts with label አባታችን ተክለሃይማኖት. Show all posts
Showing posts with label አባታችን ተክለሃይማኖት. Show all posts

Monday, May 7, 2012

አባታችን ተክለሃይማኖት ማለት እኒህ ናቸው=+=በታምራት ፍስሃ=+=

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን፡፡


            አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት የክርስቶስ ፍቅር ብልጫ ሆኖባቸዋልና ፡ ክርስትናቸውም የጣኦትን አምልኮ ተፀይፋለችና እኔ ክርስቲያን ነኝ በማለት የወንጌሉን የቃል ትምህርት በህይወት እየኖሩ አልጫ ለሆነው አለም ጨው ፡ በጨለማ ላለው ህዝብ ብርሃን ሆነው በኢትዮጵያ ከሰሜን እስከደቡብ ከምእራብ እስከ ምስራቅ ወንጌልን በቃልና በተግባር እያስተማሩ ዞሩ ፤ አለምን ንቀዋታልና ሃብትንና ስልጣንን ገፍተው ስለክርስቶስ በዱር በገደል በገዳም በዋሻ ይኖሩ ዘንድ ራሳቸውን ግድ አሉ፡፡ በነገስታት ቤት በቅምጥል ከመኖር ይልቅ ስለክርስትናው የነፃነትና የህይወት ምስክርነት በጣኦት አምላኪወች ፊት በሃዋርያት ድፍረት በሰወች ፡ በእንስሳትና በእፅዋት ላይ አድሮ ክርስቶስን ያስካደውን ፡ እግዚአብሄርን ያስረሳውን የዲያቢሎስ ሰራዊት በፅድቅ ታገሉት ፡ በወንጌሉ ሃይል ድል ነሱት ፡ በክርስቶስ ቃል አሳፈሩት ፡ በጨለማ ይንከላወስ ለነበረው ህዝብም ክርስቶስን ሰበኩላቸው ፡ በስላሴ ስም አጠመቋቸው ፡ የክርስቶስን ቅዱስ ስጋ ክቡር ደም አቀበሏቸው ፡ ዳግመኛም ቤተክርስቲያንን አሳንፀው ፡ ምእመናን መልሰው ወደጣኦት አምልኮ ወደሃጢአትም እንዳይመለሱ ፡ ካህናት አባቶችን እንዲጠብቋቸው  እያዘጋጁላቸው ለህዝቡ ሁሉ ሃዋርያ ሆነው ኖሩ፡፡

FeedBurner FeedCount