Showing posts with label ዘወረደ ሰኞ. Show all posts
Showing posts with label ዘወረደ ሰኞ. Show all posts

Wednesday, February 26, 2014

ዘወረደ ዘሰኑይ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 16 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡-  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ ጸልዩ እምቅድመ ንባበ ዝንቱ ክርታስ

የብሉይ እና የሐዲስ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ከጸዋትወ ዜማ መጽሐፍቱ አንዱ በሆነው የድጓ ክፍል ጾመ ድጓ (በጾም ስለሚደረስ ጾመ ድጓ ተብሏል) ስለ ጾም ብዙ ጽፏል። ዛሬ ታዲያ እኔ የምፈቅደው እዚህ ያንን ሰማያዊ ዜማ ስለ ጾም በጾም ለጾመኞች እየተዜመ ብንሰማው ነበረ።ነገር ግን አሁን እሱን ማድረግ አንችልም። ነገር ግን ምንም እንኳን አባታችን በዜማ ያስተላለፈውን መልእክት በጽሁፍ መግለጤ ሰማያዊውን መልእክት ዋጋ እንዳያሳጣው ቢያስፈራኝም በጌታ ባለን ድፍረት እያነበብነው ለፍሳችን በነባቢት ባህሪይዋ ዜማውን እንድትሰማው እርሱ እንዲፈቅድ እየጸለይን ዛሬ ከሰኞ ዘወረደ ድርሰቱ በጥቂቱ የተመረጡ የጾም ቃላትን እያነበብን እንማማራለን። ግእዙን ብጽፈው የሀይለ ቃሉን ኀይል በተረዳነው ነበረ። ነገር ግን ይገባን ዘንድ በአማረኛ እስከገለጠልን ድረስ እናየዋለን

FeedBurner FeedCount