Showing posts with label ፈቃደ እግዚአብሔር (ክፍልአንድ). Show all posts
Showing posts with label ፈቃደ እግዚአብሔር (ክፍልአንድ). Show all posts

Friday, July 19, 2013

ፈቃደ እግዚአብሔር (ክፍልአንድ)

በዲ/ን ብርሃኑ አድማስ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ- በድጋሜ የቀረበ ጽሑፍ)፡- በአሁኑ ጊዜ በምንኖረው ሕይወት ከፍተኛ ግራ መጋባት ከሚፈጥሩብን ነገሮች ውስጥ ፈቃደ እግዚአብሔርን የተመለከተው ቀዳሚ ሥፍራ የሚወስድብን ይመስለኛል፡፡የምናዝንባቸው፣ የምንበሳጭባቸው፣ መደረጋቸውን መቀበል እስከሚያቅተን ድረስ የምንረበሽባቸው ድርጊቶች በተፈጸሙ ጊዜ መፈተናችን ይጨምራል፡፡ ነገሮቹ በቤተ ክርስቲያን አካባቢ ሲሆኑ ደግሞ የበለጠ እንፈተናለን፡፡ እንዲያውም አንዳንድ ጊዜ ወይ እምነታችን የተሳሳተ ካለበለዚያም እግዚአብሔር የእኛን ጸሎት መስማት ያቆመ ይመስለናል፡፡ እንደዚህ ዓይነት ስሜቶች ደግሞ መቋሚያቸው ይህ ብቻ አይደለም፤ ከፍተኛ ጥራጣሬ ላይ ጥለውን ብቻ ሳይሆን ደስታችንንም ሰርቀውብን አጎረምራሚና ወቃሽ አድረገውን፤ በቤተ ክርስቲያናችንና በአንዳንድ የቤተ ክርስቲያን አካላትም ላይ እንድናኮርፍ አድርገውን በአጠቃላይ  መንፈሳዊ ሕይወታችንም ላይ ከፍተኛ ጫና ፈጥረውብን ያልፋሉ ወይም እኛን ወደ ሌላ ሕይወት ያሳልፉናል፡፡ በተለይ በእነዚህ ጊዜያት ‹‹ የእግዚአብሔር ፈቃድ›› ነው ተቀበሉ የሚል ሰው ከገጠመን ልናደምጠው እንቸገራለን፤አንዳንዴማ ልባችንን ዘልቆ ከገባው ሐዘን የተነሣ የሚናገርን ሰው ሞኝነቱ ብቻ ሳይሆን በእኛ ኅሊና የተሳለው አላዋቂነቱም እየታየን ብስጭታችን ሊጨምር ይችላል፡፡ ለመሆኑ ክፉ ሰዎች ግፍ ሲፈጽሙ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ማታለልና ተንኮል ሲፈጸም ይህን ሁሉ ፈቃደእግዚአብሔር ነው ብሎ መቀበል ይቻላልን? የፈቃደ እግዚአብሔር ድንበሩስ ምንድን ነው? ክፉ ሰዎች ሲሾሙ፣በሀገርና በሕዝብ ላይ አስከፊ ነገር ሲፈጸም አደጋና ጥፋት ሲደርስስ ፈቃደ እግዚአብሔር ነው ማለት ይቻላል? የምንፈልገው መልካም ነገር የማይፈጸመውስ ለምንድን ነው? እግዚአብሔር በጎው እንዲፈጸም አይወድምን? ወይስ ፈቃዱ የሚሆነው መቼ ነው?እነዚህ ሁሉ ለመንፈሳዊ ሕይወታችን ጥያቄዎች ሆነው የሚያስቸግሩበት አጋጣሚ ብዙ ነው፡፡ ጉዳዮቹን በቀጥታ ከማየታችን በፊት ፈቃደ እግዚአብሔርን ለመቀበል የሚፈትኑን ነገሮች እናስቀድም፡፡

FeedBurner FeedCount