Showing posts with label “ሦስቱ የኃጢያት አለቆች” ማቴ ፬፥፩-፲፩. Show all posts
Showing posts with label “ሦስቱ የኃጢያት አለቆች” ማቴ ፬፥፩-፲፩. Show all posts

Thursday, March 3, 2016

“ሦስቱ የኃጢያት አለቆች” ማቴ ፬፥፩-፲፩



ዳዊት ተስፋይ
ከተክለ ሳዊሮስ ሰ/ት/ቤት
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 24 ቀን፣ 2008 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
        ኃጢያት ኃጥአ አጣ ከሚለው የግዕዝ ግስ የተገኘ ሲሆን ማጣት ማለት ነው፡፡አንድ ሰው ኃጢያትን ሲሰራ እግዚአብሔርን ፣ እናቱን ቅድስት ድንግል ማርያምን ፣ ቅዱሳኑንና ፣ የከበረች መንግስቱን ያጣልና ኃጢያት ማጣት የሚል ትርጉም ተሰጥቶታል፡፡ በዓለም ላይ ብዙ አይነት ኃጢያቶች ቢኖሩም እናታችን ቅድስት ቤ/ክ ኃጢያቶች ሁሉ ሦስት አለቆች እንዳሏቸው ታስተምራለች፡፡ እነዚህም ስስት ፣ ትዕቢትና ፍቅረ ነዋይ ናቸው፡፡ እነዚህ ኃጢያቶች ‹‹አለቆች›› መባላቸውም የሁሉም ኃጢያቶች መገኛ ስለሆኑና እነዚህን ሦስቱ ኃጢያቶች ድል ያደረገ ሌሎቹንም ኃጢያቶች ድል ያደርጋልና ነው፡፡ ለዛሬ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በገዳመ ቆሮንቶስ ‹‹ሦስቱን የኃጢያት አለቆች›› እንዴት ድል እንዳደረጋቸውና እኛም እንዴት ድል ልናደርጋቸው እንደምንችልና እንዲሁም ታሪኩ ለመንፈሳዊ ሕይወታችን ምን ትምህርት እንደምናገኝበት የቅዱሳን አባቶቻችንን ትርጓሜ መነሻ አድርገን በአጭሩ እንነጋነጋለን፡፡ ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ ታሪኩን እንዲህ እያለ መተረክ ይጀምራል፡- “ማቴ ፬፥፩ ከዚህ በኋላ ከዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ መንፈስ ጌታችንን ኢየሱስን ወደ ምድረ በዳ ወሰደው ፤ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጾመ ፤ ከዚህም በኋላ ተራበ ”፡፡

FeedBurner FeedCount