Thursday, December 17, 2015

ቅዱስ አግናጥዮስ ምጥው ለአንበሳ (2)


በሥርጉተ ሥላሴ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ታኅሳስ 07 ቀን 2008 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

ሰማዕትነቱ


ቅዱስ አግናጥዮስ የአንጾኪያ ቤተ ክርስቲያን ጳጳስ በነበረበት ወቅት ቤተ ክርስቲያን ከዓላውያን የሮማ ነገሥታት ከፍተኛ መከራና ስቃይ ይደርስባት ነበር:: በድምጥያኖስ ዘመነ መንግሥት ከነበረው የመከራ ማዕበል በጾም እና በጸሎት፣ በብዙ መንፈሳዊ ተጋድሎ፥ በተለይም ምእመናን መከራውን ተሰቅቀው ከሃይማኖት እንዳይወጡ ተግቶ በማስተማር እንደ መልካም ካፒቴን ሆኖ ቤተ ክርስቲያንን መርቶ አሻግሯል:: ቅዱስ አግናጥዮስ ከትሕትናው የተነሣ ስለ ራሱ ሕይወት እውነተኛ የክርስቶስ ፍቅር ላይ ገና አልደረስኩም፤ እውነተኛ የደቀ መዝሙርነት ፍጽምና ላይ አልደረስኩም እያለ ያዝን ነበር:: በመሆኑም ሰማዕትነት የበለጠ ወደ እግዚአብሔር እንደሚያቀርብ በማመን ለሰማዕትነት ክብር እንዲበቃ በእጅጉ ይመኝ ነበር::

Friday, December 11, 2015

አዲስ መጽሐፍ በቅርብ ቀን


(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ታኅሳስ 2 ቀን፣ 2008 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

ውድ የመቅረዝ ዘተዋሕዶ አንባቢያን! እንደ ምን ሰነበታችሁ? ላለፉት አምስት ሳምንታት ገደማ በመቅረዝ ላይ አዲስ ጽሑፍ ሳልለጥፍ በመቆየቴ ይቅርታ እጠይቃለሁ፡፡ እንዲህ የኾንኩበት ዋና ምክንያት ግን ላለፉት ስድስት ወራት ስተረጉመው የቆየሁትንና ከቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ አያሌ መጻሕፍት አንዱ የኾነው የኦሪት ዘፍጥረት የመጀመሪያ ቅጽ መጽሐፍን የመጨረሻዉን ቅርጽ ለማስያዝ ብሎም ወደ ኅትመት ለማስገባት በነበረብኝ ጫና ምክንያት ነው፡፡ እንደ እግዚአብሔር ቅዱስ ፈቃድ በእኔ ዓቅም በብዙ ድካም የተተረጎመው ይህ አዲስ መጽሐፍ በቅርብ ጊዜ ወደ እናንተ ይደርሳል፡፡ ለማቆያ ያህልም ከመጽሐፉ መቅድም ከዚህ በታች አቅርቤላችኋለሁ፡-

Wednesday, November 4, 2015

የዓርብ ፍጥረታት



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ጥቅምት 25 ቀን 2008 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ትምህርተ ሃይማኖት - ክፍል 18
ዓርብ ዐረበ ከሚለው የግእዝ ቃል የተገኘ ሲኾን ተካተተ ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ዓርብ ማለት መካተቻ መደምደሚያ ማለት ነው። ምዕራብ ስንል መግቢያ፣ መጥለቂያ (ለምሳሌ የፀሐይ መግቢያን ምዕራብ እንደምንለው) ማለት ሲኾን ዐረብ ሲባልም ተመሳሳይ ነው - ከኢየሩሳሌም ምዕራባዊ አቅጣጫ ያሉ ሀገራት የዐረብ ምድር ይባላሉና። ዐርብ የተባለበት ምክንያት በዕለተ እሑድ መፈጠር የጀመሩት ፍጥረታት ተፈጥረው ያበቁበት፣ የተካተቱበት ቀን ስለ ኾነ ነው፡፡
በዚህ ቀን እግዚአብሔር “ምድር ሕያዋን ፍጥረታትን እንደ ወገኑ እንስሳትን ተንቀሳቃሾችን የምድር አራዊትንም እንደ ወገኑ ታውጣ” ብሎ አዘዘ /ዘፍ.1፥24/፡፡ በዚሁም መሠረት ልክ እንደ ሐሙስ ፍጥረታት በእግራቸው የሚሔዱ፣ በልባቸው የሚሳቡና በክንፋቸው የሚበሩ ፍጥረታት ናቸው፡፡ የሐሙስና የዓርብ መኾናቸውን የምንለየውም በአኗኗራቸውና በግብራቸው ሲኾን የሐሙስ ፍጥረታት በባሕር፣ የዓርብ ፍጥረታትም በየብስ ይኖራሉ፡፡ በዚህ ቀን በአራተኛ አዳምን ፈጥሯል። ይህንን በኋላ እንመለስበታለን፡፡
በሳይንሳዊ መንገድ ሔደን ምድር እነዚህን ፍጥረታት እንዴት ልታስገኛቸው ቻለች ብለን ብንጠይቅ መልስ የለውም፡፡ የተገኙት እግዚአብሔር ስላዘዘ ብቻ ነው፡፡ እግዚአብሔር ምድሪቱን አዘዛት፤ እርሷም አረገዘች፤ ወለደቻቸውም፡፡ ዛሬም ይህ እውነት እንደ ኾነ የምናይበት ኹናቴ አለ፡፡ ዝናብ ወደ ሰኔ አከባቢ መዝነብ ሲጀምር አስቀድመን ያላየናቸው ፍጥረታት ከምድር ወጥተው ሲበሩ፣ እንዲሁም እንደ እንቁራሪት ያሉ ፍጥረታት ወደ መኖር ሲመጡ እናያቸዋለን፡፡ አስቀድሞ ባልተጣለ ዕንቁላል የተለያዩ ዓይነት ትላትሎች ከጭቃ ውስጥ ሲፈጠሩ እናያቸዋለን፡፡ እንግዲህ የእግዚአብሔርን ጥበብ ታያላችሁን?

Tuesday, October 27, 2015

ቅዱስ አግናጥዮስ ምጥው ለአንበሳ (1)



በሥርጉተ ሥላሴ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ጥቅምት 16 ቀን 2008 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
እንደ ቤተ ክርስቲያን ትውፊት፥ ቅዱስ አግናጥዮስ ጌታችን ደቀ መዛሙርቱን ስለ ትሕትና ለማስተማር በመካከላቸው ያቆመው ሕፃን ነው፡፡ ከዚህም የተወለደበትን ዘመን መገመት ይቻላል (30-35 ዓ.ም.)፡፡ በጌታችን ደቀ መዛሙርት መካከል በመንግሥተ ሰማያት ከሁሉ የሚበልጥ ማን ነው?” የሚል ክርክር በተነ ጊዜ፥ ጌታ ሕፃኑን ቅዱስ አግናጥዮስን አቅፎ በመሳም፡- ተመልሳችሁ ከየውሀት ጠባይዓዊ ደርሳችሁ እንደዚህ ሕፃን ካልሆናችሁ መንግሥተ ሰማያት አትገቡም አላቸው፥ “ሕፃንንም ጠርቶ በመካከላቸው አቆመው እንዲህም አለ፥ እውነት እላችኋለሁ ካልተመለሳችሁ እንደዚህም ሕፃን ካልሆናችሁ ወደ መንግሥተ ሰማያት ከቶ አትገቡም . . . ” እንዲል /ማቴ.18፥2-5፣ አንድምታ ወንጌል/፡፡ ሰማይና ምድርን ፈጥረው በተሸከሙ እጆች፣ ሕዝብና አሕዛብን ለማዳን ግራ ቀኝ በተዘረጉ ቅዱሳት ክንዶች መታቀፍ ምንኛ መቀደስ ነው?! ቅዱስ አግናጥዮስ ጌታችን በመንግሥተ ሰማያት ከሁሉ የሚበልጥ ሕፃን ብሎ እንደመሰለለት እንደዚያው እንደ ምሳሌው ሆኖ እስከ መጨረሻ ሕይወቱ በየውሀት ጠባይዓዊ የኖረ፣ ጌታ አቅፎ እንደ ተሸከመው እርሱም ጌታውን በልቡናው የተሸከመ ቅዱስ አባት ነው፡፡ ስለዚህም ቅዱስ አግናጥዮስ ራሱን በተደጋጋሚ ቲኦፎረስ (Theophorus - እግዚአብሔርን በልቡናው የተሸከመ፣ ለባሴ እግዚአብሔር)ስቶፎረስ (Chritophorus - ክርስቶስን በልቡናው የተሸከመ፣ ለባሴ ክርስቶስ) እያለ ይጠራ ነበር፤ በጣም ደስ የሚሰኝበት ሙም ነበር፡፡ ለዚህም ነው በመጨረሻ ለተራቡ አናብስት ተጥሎ ሰማዕትነቱን በፈጸመበት ሰዓት አናብስት ሌላውን አካሉን በመላ ሲበሉ ልቡን መርጠው የተ፡፡

FeedBurner FeedCount