Showing posts with label ለይሖዋ ምስክሮች ኑፋቄ የተሰጠ ምላሽ (ክፍል አራት). Show all posts
Showing posts with label ለይሖዋ ምስክሮች ኑፋቄ የተሰጠ ምላሽ (ክፍል አራት). Show all posts

Tuesday, December 30, 2014

ለይሖዋ ምስክሮች ኑፋቄ የተሰጠ ምላሽ (ክፍል አራት)



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ማግሰኞ ታኅሳስ 21 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

የሥላሴ ትምህርት በጕባኤ ኒቅያ አበው
 ውድ የመቅረዝ ተከታታዮች እንደምን ሰነበታችኁ? በጥያቄና መልስ ዓምዳችን ለይሖዋ ምስክሮች የስሕተት ትምህርት ኦርቶዶክሳዊ ምላሽ መስጠት ከዠመርን የዛሬው አራተኛው ክፍል ነው፡፡ በክፍል አንድ ምላሻችን የይሖዋ ምስክሮች የስሕተት ትምህርቶች ምን ምን እንደኾኑ፥ እንዲኹም መሠረታዊ የምሥጢረ ሥላሴን ትምህርት በመጠኑ ዐይተናል፡፡ በክፍል ኹለት ክፍለ ጊዜአችንም ከብሉይ እና ከሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት በማመሳከር ምሥጢረ ሥላሴ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርት እንደኾነ ተመልክተናል፡፡ በክፍል ሦስትም ከሐዋርያነ አበው ዠምረን እስከ ሦስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበሩ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ምን ብለው እንዳስተማሩ ተመልክተናል፡፡ ስለ ቅድስት ሥላሴ የመጨረሻው ክፍል በኾነው በዛሬው ምላሻችን ደግሞ በአጠቃላይ በጕባኤ ኒቅያ የነበረውን ሒደትና ውሳኔ እንመለከታለን፡፡ ይኽን የምናደርግበት ምክንያትም በክፍል ሦስት ምላሻችን እንደነገርናችኁ የይሖዋ ምስክሮች የሥላሴ ትምህርት የተወሰነው በ325 ዓ.ም. በጉባኤ ኒቅያ በንጉሥ ቈስጠንጢኖስ አስገዳጅነት ነው ስለሚሉ ነው፡፡ እግዚአብሔር ዓይነ ልቡናችንን ያብራልን አሜን!!!

FeedBurner FeedCount