Showing posts with label ልዩ ፍርድ ቤት-. Show all posts
Showing posts with label ልዩ ፍርድ ቤት-. Show all posts

Friday, June 15, 2012

ልዩ ፍርድ ቤት- በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ!!


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
  “የብዙዎቻችን ከንፈሮች ለሐሜት የተከፈቱ ናቸው፡፡ የራሳችንን ግንድ ትተንም ከሰዎች ጉድፍን ለማውጣት እንዳዳለን፡፡ በወንድሞቻችንም ላይ እንፈርዳለን፡፡ ተወዳጆች ሆይ! እንጠንቀቅ! የፍርድ ዙፋን ያለው ከእርሱ ጋር ብቻ ነውና የወልድን ሥልጣን እኛው አንያዘው፡፡
መፍረድ ትፈልጋላችሁን? እንግዲያስ ምንም የማያስወቅስና በጣም ብዙ ጥቅም ያለው የፍርድ ችሎት አለላችሁ፡፡ አጥብቃችሁ በራሳችሁ ላይ ለመፍረድ ተቀመጡ፡፡ አስቀድማችሁ በደላችሁን ከፊታችሁ በመዝገብ አስቀምጡት፤ የነፍሳችሁም ወንጀል በሙሉ መርምሩ፤ ተገቢውንም ፍርድ አስቀምጡና ነፍሳችሁንይህንና ያንን በደል ያደረግሺው ለምንድነው?በሏት፡፡ ከዚህ ፈቀቅ ብላ የሌሎችን ሰዎች ኃጢአት መፈለግ ከጀመረችየተከሰስሽበት ጉዳይ የእነዚያ አይደለም፣ አንቺም የመጣሽው ስለነዚያ ሰዎች ለመሟገት አይደለም፡፡ ስለምንድነው ክፋትን የሠራሽው? ስለምንስ ነው ያንንና ይህን ጥፋት ያጠፋሽው? የራስሽን ተናገሪ እንጂ ሌሎችን አትውቀሺበሏት፡፡ ሁል ጊዜም ይህን አስጨናቂ ፈተናን እንድትመልስ አቻኩሏት፡፡ ተሸማቅቃ ምንም የምትመልሰው ነገር ከሌላትም አስፈላጊውን ቅጣት (ቀኖና) ወሱንባት፡፡ ይህን ልዩ ፍርድቤት ሁል ጊዜ የምትቀመጡ ከሆነ የእሳት ሸሎቆው፣ መርዘኛው ትልና ሊመጣ ያለውን ስቃይ በአእምሮዋችሁ እንዲቀረፅ ይረዳችኋል፡፡

ሁልጊዜምእሱ ወደ እኔ መጥቶብኝ ነው፤ እሱ ሸውዶኝ ነው፤ እሱ ፈትኖኝ ነውእያለች ከዲያብሎስ ጐን እንድትሰለፍና ሐፍረት የለሽ ንግግሮችን እንድትናገር አትፍቀዱላት፡፡ ይልቁንምአንቺ ፍቃደኛ ባትሆኚ ነው እንጂ እነዚህ ሁሉ ካንቺ ጋራ ምንም ጉዳይ የላቸውምብላችሁ ንገሯት፡፡እኔ እኮ ሥጋ ለባሽ ነኝ፣ የምኖረውም በምድር ነውካለቻችሁምይህ ሁሉ ሰበብና ምክንያት ነው፡፡ ብዙዎች አንቺ የለበስሽውን ሥጋ

FeedBurner FeedCount