Showing posts with label መስቀል ኃይል. Show all posts
Showing posts with label መስቀል ኃይል. Show all posts

Saturday, September 26, 2015

መስቀል ኃይል

በልዑል ገብረ እግዚአብሔር
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መስከረም 15 ቀን 2008 ዓ.ም.)፦ በስመ አብ ወወልድ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

የአዳም ነገር……
በቀራኒዮ መሐል ቀጠሮ ተይዞለታል
የገመጣት ፍሬ መዘዝ ወልዳ
ከሰገነት……...ቁልቁል ሰድዳ
ብርሃን ልብሱ ተገፎበት
ልበ ምቱ……..ቀንሶበት
ክብሩን ሊመልስለት
…….የማይሻረው ቃልን ሰጥቶታል!

የእሳት አጥር ጉድጓድ ጨለማ ቤት ሰፍፎ
ለዚህ አልነበረም…….ተፈጥሮው
በሲኦል ከተማ መጋኛ ሊመታው
ያ የሰው በኩር የፊጥኝ ታስሮ
በዲያቢሎስ ቀንበር ተቀንብሮ
እሳቱን ሲያሳርሰው በጅራፍ ጀርፎ
ባርነትን ተፈራርመው
………………..ፀጋ ልብሱን ገፍፎ ገፍፎ!

ዋይ! ዋይ! ዋይ!
የሲቃ ድምፀት ምህረት የለሹ እኩይ ግዛት
አዳም እንጂ የተጎዳ…
እበላለው ብሎ የተበላ
…………..እወጣለው ብሎ የወረደ
በፍቃዱ …….
ከግዛቱ ወደ ግዞት ተሰደደ ተዋረደ

FeedBurner FeedCount