Showing posts with label ማርታም ታገለግል ነበር. Show all posts
Showing posts with label ማርታም ታገለግል ነበር. Show all posts

Tuesday, March 22, 2016

ማርታም ታገለግል ነበር


                                                በዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
(ከመጽሐፈ ገጹ የተወሰደ)
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 13 ቀን 2008 ..)- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ማርያምና ማርታ እኅትማማቾች ናቸው፡፡ኢየሱስም ማርታንና እኅትዋን አልዓዛርንም ይወድ ነበር› (ዮሐ. 115) ስለዚህም በቢታንያ በሚገኘው ቤታቸው እንግዳ ሆኖ ተገኘ፡፡ እጅግ ለሚወዱት ጌታ ፍቅራቸውን ለመግለጽ እኅትማማቾቹ ይሻላል ብለው ያሰቡትን ሁለት የተለያየ ዓይነት አቀባበል አድርገውለት ነበር፡፡ ማርታ ለምትወደው እንግዳዋ ምግብ ለማቅረብ ብዙ ተጨንቃ በጓዳ ሥራ ላይ ተወጠረች፡፡ለታላቁ ጌታ ምን ላቅርብለት ይሆን?› ብላ ተጠበበች፡፡ መቼም የምናከብረው ሰው እንግዳ ሆኖ ሲመጣ ሙያውም ሊጠፋብን ይችላል፡፡ ማርታም የገጠማት ይኼው ነው ምኑን ከምኑ አድርጋ እንደምታቀርብ ግራ ገባት ጌታችን እንዳለውበብዙ ነገር ተጨነቀች ታወከች፡፡

FeedBurner FeedCount