Showing posts with label ምክረ አበው -ቁጥር ሦስት. Show all posts
Showing posts with label ምክረ አበው -ቁጥር ሦስት. Show all posts

Wednesday, September 19, 2012

ምክረ አበው -ቁጥር ሦስት


1. ከዕለታት በአንድ ቀን አባ ፓምቦ አባ እንጦንስን “ማድረግ ያለብኝ ነገር ምንድነው?” ብሎ ይጠይቋል፡፡ አባ እንጦንስም እንዲህ ሲል መለሰለት “በራስህ ጽድቅ አትታመን፤ ላለፈው አትጨነቅ፤ ይልቁኑ አንደበትህንና ሆድህን ግዛ፡፡”
2. አባ እንጦንስ በአንድ ወቅት እንዲህ አለ፡- “በዚህች ምድር ላይ ስንኖር ሕይወታችንንም ሆነ ሞታችን ከባልንጀራችን ጋር ነው፡፡ ወንድማችንን ገንዘብ ካደረግነው እግዚአብሔርን ገንዘብ እናደርጓለን፤ ወንድማችንን ካስቀየምነው ግን በክርስቶስ ላይ ኃጢአትን እንሠራለን፡፡”

FeedBurner FeedCount