Showing posts with label ሥጋ ሥጋት ሲኾን. Show all posts
Showing posts with label ሥጋ ሥጋት ሲኾን. Show all posts

Tuesday, August 20, 2013

ሥጋ ሥጋት ሲኾን

በዲ/ን ብርሃኑ አድማስ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ ነሐሴ ፲፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም)፡- ከኢትዮጵያ ውጭ ለመኖር በኹኔታዎች ተገድዶ ወደ ጀርመን የሔደ አንድ ወንድማችን በሚኖርበት ሀገር እጅግ በሽተኛ ኾኖ ይቸገራል፡፡ ጾም አይጾም፤ ምግብ አይመርጥ የነበረው ሰው የፈለገውን ቢያደርግም ለጤናው ሽሎት ያጣል፡፡ በሚኖርበት ሀገር በሕክምና ዕውቀት በጣም ያደገ ስለነበር እጅግ ብዙ ሙከራዎችን ቢያደርግም ተስፋ ያጣል፡፡ በመጨረሻ በአመጋገብ ብቻ ሕክምና ወደምታደርግ ስፔሻሊስት ሐኪም ይላካል፡፡ ሐኪሟም የበሽተኛውን የሕማም ታሪክ ጊዜ ወስዳ በተደጋጋሚ ካጠናች በኋላ ሕክምናውን ለመጀመር ኹለት ዝርዝሮች አዘጋጅታ ጠበቀችው፡፡ ከዝርዝሮቹ አንደኛው ሊመገባቸው የሚገባውን የምግብ ዐይነቶች የያዘ ሲኾን ኹለተኛው ደግሞ ሊመገባቸው የማይገባውን የያዘ ነበር፡፡ ዝርዝሩን ይዞ ወደ ቤቱ በመሔድ በትእዛዙ መሠረት መዳኑን እየተጠባበቀ መመገብ ጀመረ፡፡ ለውጡን በመጠኑ እያየ ደስ እያለው ሳለ እንዲበላቸው የታዘዛቸው ምግቦች ቀደም ብሎ በብዛት ከሚመገባቸው የተለዩ ስለነበሩና ቀድሞ በብዛት ይመገባቸው የነበሩት ደግሞ ከተከለከላቸው ውስጥ ስለነበሩ ኹኔታዉን ደጋግሞ ሲመለከት አንድ ነገር ይከሰትለታል፡፡ የተከለከላቸው ምግቦች በሙሉ ሲያያቸው በሀገር ቤት በፍስክ የሚበሉት ሲኾኑ እንዲመገባቸው የታዘዙለት ደግሞ በሙሉ የጾም ምግብ ከሚባሉት ኾነው ያገኛቸዋል፡፡ በኹኔታው በጣም ከተገረመ በኋላ “የጾም ምግብ ለጤና ተስማሚ ከኾነ ለምን አልጾምም?” ይልና ፈጽሞ ረስቶት የነበረውን ጾም ድንገት በሰኔው የሐዋርያት ጾም ይጀምራል፡፡ ልክ አንድ ሳምንት ከጾመ በኋላ ኹል ጊዜም እንደሚያደርገው ለክትትል ወደ ሐኪሙ ያመራል፡፡ የላባራቶሪ ውጤቶቹ ሲመጡ በተለይ እነ ደም ግፊት፣ ስኳርና የመሳሰሉት በሽታዎች በከፍተኛ ኹኔታ ቀንሰዋል፡፡

FeedBurner FeedCount