Showing posts with label ቅዱሳት መጻሕፍት ስለማንበብ. Show all posts
Showing posts with label ቅዱሳት መጻሕፍት ስለማንበብ. Show all posts

Thursday, February 12, 2015

ቅዱሳት መጻሕፍት ስለማንበብ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐሙስ የካቲት 5 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
እስኪ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ መጽሐፍ ቅዱስን ላለማንበብ ምክንያት ይደረድሩ ለነበሩ ሰዎች ይሰጣቸው የነበረውን ተግሣፅ ከዚኽም ከዚያም ያሰባሰብኩትን አንድ ላይ አድርጌ ላካፍላችኁና ራሳችንን እንመርምርበት፡-
·        መጽሐፍ ቅዱስ የለንም የሚሉ ነበሩ፡፡ ይኽም በጣም ውድ ስለኾነ ነው፡፡ 4ኛው ... አንድን ሙሉ መጽሐፍ ቅዱስ ለመግዛት የአንድ ዓመት ደመወዝ ነበርና፡፡ ሊቁ ግንይኽ ምክንያት አይኾንም፡፡ ብያንስ መጽሐፍ ቅዱስ ሙሉው ባይኖራችኁም ከወንጌል አንዱን ብቻ መግዛት ትችላላችኁ፤ ርሱንም ዘወትር ማንበብ ትችላላችኁይላቸው ነበር፡፡ይኽን ማድረግ ባትችሉ እንኳን ዘወትር ወደዚኽ ጕባኤ በመምጣት በነጻ መማር ትችላላችኁ፡፡ ብያንስ ወደ ቅዳሴው ኑ፡፡ እዚያ የሚነበበውንና የሚተረጐመውን በሥርዓት አዳምጡ፡፡ ወዮ! እዚኽ ስትመጡ ትቁነጠነጣላችኁ፤ ሙቀቱ ብርዱ ትላላችኁ፡፡ ወደ ገበያ ቦታ፣ ወደ ተውኔት፣ ወደ ስታድዬም ስትሔዱ ግን ምንም አይመስላችኁም፡፡ ዶፍ ዝናብ ቢዘንብባችኁ፣ ሙቀቱ አናትን የሚበሳ ቢኾን፣ በውኃ ጥም ብትያዙ ትቋቋማላችኁ፡፡ ታድያ ምን ዓይነት ይቅርታ ይኾን የሚደረግላችኁ?” ይላቸው ነበር፡፡

FeedBurner FeedCount