Showing posts with label ቅዱስ ቀሌምንጦስ ዘሮም. Show all posts
Showing posts with label ቅዱስ ቀሌምንጦስ ዘሮም. Show all posts

Friday, October 2, 2015

ቅዱስ ቀሌምንጦስ ዘሮም



በሥርጉተ ሥላሴ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መስከረም 21 ቀን 2008 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
በጥንታዊቱ ቤተ ክርስቲያን ሐዋርያትን አህለው ሐዋርያትን መስለው ከተነሡ እጅግ ከሚታወቁት ሐዋርያነ አበው መካከል፥ የቅዱስ ጴጥሮስና የቅዱስ ጳውሎስ ደቀ መዝሙር የነበረው ቅዱስ ቀሌምንጦስ ዘሮም አንዱ ነው፡፡ ስለዚሁ ቅዱስ ሰው ብዙ ዓይነት አመለካከት ያለ ሲኾን፥ አውሳብዮስ ዘቂሳርያ፣ አባ ጀሮም እና ሌሎች አርጌንስን ተከትለው የቅዱስ ጳውሎስ ደቀ መዝሙር እንደ ነበረ ያስተምራሉ /ፊልጵ.4፥3/፡፡ “የንጉሥ ድምጥያኖስ የአጎት ልጅ ነው” የሚሉም ያሉ ሲኾን፣ ሌሎች ደግሞ “እጅግ ጥበበኛና የተማረ ሰው የነበረና በኋላም ዕውቀትን ፍለጋ ወደ ፍልስጥኤም ሲሔድ ከቅዱስ ጴጥሮስ ጋር ተገናኝቶ ክርስቲያን ኾኗል” ይላሉ /አባ ቴዎድሮስ ያ.ማላቲ፣ ሐዋርያነ አበው፣ ገጽ 64/
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ. ሊቃውንት የሚታመነውና ሕዳር 29 የሚነበበው ስንክሳር እንደሚነግረን ደግሞ፥ ቀሌምንጦስ ዘሮም ትውልዱ ከንጉሣውያን ቤተ ሰቦች ነው:: አባቱ “ቀውስጦስ” የሮማው ንጉሥ የጦር አለቃ የነበረ ሲን፥ በቅዱስ ጴጥሮስ ስብከት አምኗል:: በአንድ ወቅት “ቀውስጦስ” ወደ ሮማው ንጉሥ ዶ ለብዙ ቀናት ቢዘገይ ወንድሙ ሚስቱን ለማግባት ፈለገ:: የቀሌምንጦስ እናት ይህንን ማ ቀሌምንጦስንና ታናሽ ወንድሙን ይዛ አባታቸው እስኪመለስ ድረስ ፍልስፍና ይማሩ ብላ ወደ አቴንስ ከተማ ለመድ ተነሣች:: በመርከብ ተሳፍረው ሲዱ ሳሉ ግን ኃይለኛ ማዕበል ተነሥቶ መርከቧን ሰባበራት ንም በታተናቸው:: ቀሌምንጦስንም ከቤተ ሰቦቹ ለይቶ እስክንድርያ አደረሰው:: ቅዱስ ጴጥሮስ በእግዚአብሔር ትእዛዝ ወደ እስክንድርያ ከተማ ገብቶ ሲያስተምር ከቀሌምንጦስ በቀር አማኝ አላገኘም:: ቀሌምንጦስ የቅዱስ ጴጥሮስን ስብከት ሲሰማ በጌታችን አምኖ የክርስትና ጥምቀት ተጠመቀ፤ ከዚችም ሰዓት ጀምሮ የቅዱስ ጴጥሮስ ደቀ መዝሙር ፡፡
ቅዱስ ሄሮኔዎስ እንደሚነግረን፥ በኋላ ላይ የሮማ ከተማ አራተኛው ሊቀ ጳጳስ ኗል /በእንተ መናፍቃን፣ ሣልሳይ መጽሐፍ 3:3/፡አውሳብዮስ ዘቂሳርያም ከዚህ ተነሥቶ “ጊዜው ከ92 እስከ 101 ዓ.ም. ነው” ይላል፡፡

FeedBurner FeedCount