Showing posts with label በቃሌ ብትኖሩ በእውነት ደቀመዛሙርቴ ናችሁ. Show all posts
Showing posts with label በቃሌ ብትኖሩ በእውነት ደቀመዛሙርቴ ናችሁ. Show all posts

Wednesday, October 3, 2012

በቃሌ ብትኖሩ በእውነት ደቀመዛሙርቴ ናችሁ


    የዮሐንስ ወንጌል የ38ኛ ሳምንት ጥናት (ዮሐ.8፡21-47)
  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
 (ከቻሉ ጸልየው ይጀምሩ)
  ልበ ስሑታን የሆኑ ጸሐፍትና ፈሪሳውያን ጌታችንን ለመግደል፣ ከሕዝቡ ልብ ለማውጣት ያልፈነቀሉት ድንጋይ ያልፈለጉበት ስሕተት የለም፡፡ ሆኖም ንጹሐ ባሕርይ ነውና ይህን ያገኙበት ዘንድ አልተቻላቸውም፡፡ እግዚአብሔር ነውና በልባቸው የሚያመላልሱትን ስለሚያውቅ ኃጢአታቸውን አውቀው ፍቅሩን እንዲረዱለት፤ የታመሙትን (እነርሱን) ፍለጋ እንደመጣ እንዲያውቁለት በጥበብ፣ በኃይል እንዲሁም በሥልጣን ይነግራቸው ነበር፡፡ አንዳንድ ጊዜ በሚያስፈራሩ ቃላት ሌላ ጊዜም በሚጋብዙ የትሕትና ቃለት ያምኑበት ዘንድ ይጠራቸው ነበር፡፡ እነርሱ ግን ይህን እንዳያውቁ በምርጫቸው ልባቸውን አደንድነውታልና ይገድሉት ዘንድ ፈለጉ፡፡

FeedBurner FeedCount